Saturday, 26 September 2015 09:19

አንጋፋው የሙዚቃ ሰው መርአዊ ስጦት ተሸለሙ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

     ባለፈው ማክሰኞ 80ኛ የልደት በዓላቸውን ያከበሩት አንጋፋው ክላርኔት ተጫዋች መርአዊ ስጦት ተሸለሙ በዳኒ ሮጎ የማስታወቂያ ስራና ፊልም ፕሮዳክሽን ድርጅት አስተባባሪነት በሃርመኒ ሆቴል በተዘጋጀው አርቲስቱን የማክበርና የማመስገን ስነ - ስርዓት ላይ ልጃቸው ኢትዮጵያ መርአዊ ላለፉት 60 ዓመታት የተጫወቱበትን ክላርኔት ያበረከተችላቸው ሲሆን የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማህበርም ክብራቸውን የሚገልፅ የምስጋና የምስክር ወረቀት እንዳበረከተላቸው ተገልጿል፡፡ በእለቱ አቶ አብነት ገብረመስቀል የ50 ሺህ ብር ስጦታ ያበረከቱላቸው ሲሆን የጃዝ አምባዎቹ ያሬድ ተፈራ፣ አበጋዝ ክብረወርቅ፣ ግሩም መዝሙር፣ ሳምሶን ጃፋር፣ ፋሲል ዊሂር እና አክሊሉ ዘውዴ ለአርቲስቱ ክብር እያንዳንዳቸው ሙዚቃ ተጫውተውላቸዋል፡፡ አርቲስት ጌትነት እንየው፣ ፍቃዱ ተክለማርያምና ሙዚቀኛው ግርማ ይፍራሸዋም በየግላቸው ስጦታ ያበረከቱላቸው ሲሆን ጌትነት እንየው “ድንቅ” የተሰኘ ግጥም እንደገጠመላቸውም የዳኒ ሮጎ ስራ አስኪያጅ አርቲስት ዳንኤል ተገኝ ተናግሯል፡፡
 አቶ አብነት ገ/መስቀል አርቲስቱን እስከመጨረሻው ለመደገፍ ቃል የገቡ ሲሆን የላንድ ማርክ ሆስፒታል ባለቤት ፕ/ር ከበደ ወሌም በማንኛውም ሁኔታ ለህክምና ሲመጡ ሆስፒታላቸው በነፃ እንደሚያክማቸው ቃል ገብቷል፡፡ ቲሞኒየር ልብስ ስፌትም በእለቱ ሙሉ ልብሳቸውን በማልበስ ለአርቲስቱ ያለውን አድናቆት ገልጿል፡፡ 

Read 2017 times