Friday, 11 September 2015 09:58

ሀገር ፍቅር የ80 ዓመት ጉዞውን በዳንስ ትርዒት ያሳያል

Written by  ማህሌት ኪዳነወልድ
Rate this item
(1 Vote)

 ባለፈው ሐምሌ 80ኛ ዓመቱን ያከበረው ሀገር ፍቅር ቲያትር፤ለአዲሱ ዓመት በአል በአል የሚሸቱ ፕሮግራሞችን ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ የቲያትር ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ካሳዬ ገበየሁ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፤በበዓሉ ዝግጅት ላይ የቲያትር ቤቱን የ80 ዓመታት ጉዞ የማያሳይ የዳንስ ትርኢት ይቀርባል፡፡ አንጋፋው ድምጻዊ ጌታቸው ጋዲሳን ጨምሮ በርካታ ዕውቅ ሙዚቀኞች ሥራቸውን ለታዳሚው እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል፡፡ የአውድ ዓመት ፕሮግራሙ ከቀኑ 8፡30 እስከ 12፡30 የሚዘልቅ ሲሆን መግቢያው 30 ብር ነው፡፡

Read 1549 times