Friday, 11 September 2015 09:32

“በአዲሱ ዓመት 3 ዋነኛ እቅዶች አሉኝ” ዲያቆን ዳንኤል ክብረት (ደራሲና የቤተክርስቲያን ታሪክ ተመራማሪ)

Written by 
Rate this item
(5 votes)

     አመቱ ለኔ ጥሩ ሆኖ ነው ያለፈው፡፡ ሶስት እቅዶቼን አሳክቻለሁ፡፡ አንደኛ የማሳትማቸው መጻህፍት ነበሩ፡፡ ተሳክተውልኛል፡፡ “አራቱ ሃያላን” እና “እኛ የመጨረሻዎቹ” የተሰኙትን መጻህፍት ለአንባቢ ማድረስ ችያለሁ፡፡ ሁለተኛ የማከናውነው ጥናት ነበር፤በዓመቱ አከናውናለሁ ያልኩትን ያህል ሰርቻለሁ፡፡ “የበጎ ሰው ሽልማት;ንም አመቱ ሳይጠናቀቅ አንድ ምዕራፍ ማድረስ ነበረብኝ፤እሱም ጥሩ ደረጃ ደርሷል፡፡ በቀጣዩ አዲስ አመትም 3 ዋነኛ እቅዶች አሉኝ፡፡ አንደኛ፤#የበጎ ሰው ሽልማት”ን ተቋማዊ ማድረግ፣ ሌላው ሁለት መፅሀፍትን ለአንባቢ ማድረስ ነው፡፡ አንዱ አቡነ ተክለሃይማኖት ላይ የሚያተኩር ሲሆን ሌላው እጨጌ እመባቆምን የተመለከተ ነው፡፡ ሦስተኛው፤የጥናት ስራ ነው፡፡ የሚያተኩረውም በተለይ ጥንታዊ የሆኑ የኢትዮጵያ ቦታዎች ላይ ይሆናል፡፡ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ቦታዎችን መጠሪያ ማጥናት ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ድሮ ናዝሬት የሚባለው አሁን አዳማ ሆኗል፡፡ ልክ እንደዚህ ከ20 ዓመት በኋላ ናዝሬት የሚል ቦታ የተጠቀሰበትን መፅሀፍ የሚያነብ ልጅ ግራ ነው የሚገባው፡፡ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ጊዜ ራሱ አንዱ ክርክር የፈጠረው የቦታዎች ስም መቀያየር ነው፤ስለዚህ በዚህ ላይ ጠለቅ ያለ ጥናት ለመስራት እቅድ አለኝ፡፡ እንግዲህ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ፤መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንም እመኛለሁ፡፡

Read 4816 times