Friday, 11 September 2015 09:16

ቤተልሄም ጥላሁን ከአፍሪካ 30 የድንቅ ፈጠራ ባለቤቶች አንዷ ሆነች

Written by 
Rate this item
(6 votes)

     የታዋቂው የጫማ አምራች ኩባንያ “ሶል ሪበልስ” መስራችና ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵዊቷ የቢዝነስ ሰው ቤተልሄም ጥላሁን፤ በታዋቂው የአሜሪካ የቢዝነስ መጽሄት “ኳርትዝ” የአመቱ የአፍሪካ 30 ፈርቀዳጅ፣ የድንቅ ፈጠራ ባለቤቶች ዝርዝር ውስጥ ተካተተች፡፡ተቀማጭነቱን በአሜሪካ ያደረገው መጽሄቱ፤ ፈርቀዳጅ፣ አዲስ ሃሳብ አፍላቂና ለአካባቢያዊ ችግሮች ተስማሚ መፍትሄ የሚሰጡ ድንቅ ፈጠራዎችን አበርክተዋል ያላቸውንና ከ15 የተለያዩ የአፍሪካ አገራት የመረጣቸውን 30 ምርጦች ይፋ ባደረገበት ዝርዝር የ35 አመቷን ቤተልሄም አካትቷታል፡፡ከ10 አመት በፊት ቤተልሄም ያቋቋመችው “ሶል ሪበልስ”፣ በአሁኑ ወቅት አለማቀፍ ተፈላጊነትን ያተረፉ የጫማ ምርቶቹን ወደተለያዩ 30 የዓለማችን አገራት ኤክስፖርት እያደረገ መሆኑን የጠቆመው መጽሄቱ፤ ቤተልሄም ያመነጨችው የቢዝነስ ሃሳብ ብዙዎችን ተጠቃሚ ያደረገና ውጤታማ በመሆኑ በዝርዝሩ ውስጥ ልትካተት እንደቻለች ገልጿል፡፡

Read 3403 times