የዕንቁጣጣሽ አበባ!
-ነ.መ.
አንዳንድ ህፃን ዕድሏ፣
ያስታውቃል ከብቅሏ
አበቅቴዋ አይስትም ውሉን
ለእንቁጣጣሽ ልትወለድ፣ ተፅፏል ቃሉ
ቀድሞውን!
በአበባ ወር የመጣች፣ የዕንቁጣጣሽ አበባ
ትስቃለች ታለቅሳለች - ፣
የዕድሏን ያህል ለዕማማ!
የዕድሏን ያህል ለአባባ!!
እንኳን መጣሽ አንች አበባ፣
እንኳን መጣሽ አንች ወለባ!
የጎመንም፣ የገንፎሽም፤ ምንቸቱ
አንቺው ቤት ይግባ!!
(ለኪዳኔና ለጤና አዲሷን
የዕንቁጣጣሽ
አበባይቱን ለሚቀበሉ፣
ልጆቻቸው ሁሉ)
- ነሐሴ 29 2007 ዓ.ም.
Published in
የግጥም ጥግ