Monday, 31 August 2015 10:20

“አይፈራም ጋሜው እና ምናባዊ እንግዶቹ ቁ.2” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በሲሳይ መኳንንት የተዘጋጀው “አይፈራም ጋሜው እና ምናባዊ እንግዶቹ ቁ.2” ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ “ይህ… መፅሃፍ ከቅፅ 1 ጋር በይዘት ተመሳሳይነት ስላለው ተከታይ ክፍል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን የመጀመሪያውን መፅሃፍ አግኝቶ ለማንበብ ያልቻለ አንባቢ ቢኖር ይህን ተከታይ መፅሃፍ ብቻ በተናጠል ሊያነበው ይችላል” ብሏል - ደራሲው መቅድም በሚል ርዕስ ባሰፈረው ማስታወሻ፡፡
የቀድሞውም ሆነ የአሁኑ መፅሃፍ በንግግር ልውውጥ ላይ የተመሰረቱ ሃሳቦችን የሚያስተላልፉ መሆናቸውን የጠቆመው ደራሲው፤ ከአገር ውስጥ ከቀድሞው የአገሪቱ መሪዎች  ከኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምና ከጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር፣ ከውጭ ከኔልሰን ማንዴላ፣ ኦፕራ ዊንፍሬይ፣ ማይክል ጃክሰንና ሌሎች ታዋቂ ሰዎች ጋር ምናባዊ ቃለ ምልልስ ማድረጉን ገልጿል፡፡ መፅሃፉ ለአገር ውስጥ በ75 ብር፣ ለውጭ አገራት በ10 ዶላርና በ8 ዩሮ ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 1565 times