በቅድስት ይልማ የተደረሰውና ዳይሬክት የተደረገው #ከእለታት; ፊልም ባለፈው እሁድ ተመረቀ፡፡ የ1፡35 ደቂቃ ርዝማኔ ያለውን ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ 6 ወር እንደፈጀ ታውቋል፡፡ ፊልሙ፣ሁለት በተመሳሳይ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ወጣቶች ተፈጥሮ በአጋጣሚ የሰጠቻቸውን ስጦታ እንዴት እንደሚጠቀሙበት የሚያሳይ የቤተሰብ ድራማ ነው ተብሏል፡፡
በ123 ስቱዲዮ ተዘጋጅቶ፣በአለን ኢንተርቴይመንት በቀረበው #ከእለታት; ፊልም ላይ እፀህይወት አበባና ሩታ መንግስታብን ጨምሮ በርካታ ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና