የሰዓሊና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ “መንገድ ስጡኝ ሰፊ” የተሰኘ የግጥም መድበል ላይ በነገው ዕለት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት እንደሚካሄድበት ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ አስታወቀ፡፡
ለውይይቱ መነሻ ሃሳብ የሚያቀርቡት ገጣሚና ጋዜጠኛ ባንችአየሁ ዓለሙ ሲሆኑ የጥበብ ወዳጆች በውይይቱ ላይ እንደሚታደሙ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
በሌላ በኩል የደራሲ ገዛኸኝ ላቀው “የደቦቃ ጥንስስ” የተሰኘ መፅሀፍ በነገው ዕለት ከጠዋቱ 3 ሰዓት የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች በሚገኙበት በዚያው በብሄራዊ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ እንደሚመረቅ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ገልጿል፡፡
Saturday, 08 August 2015 09:31
“መንገድ ስጡኝ” ሰፊ ውይይት ሲካሄድበት፤ “የደቦቃ ጥንስስ” ይመረቃል
Written by Administrator
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና