Saturday, 01 August 2015 14:12

ፎክሎር” የፊታችን ሐሙስ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በሰለሞን ተሾመ ባዬ የተዘጋጀው “ፎክሎር ምንነቱና የጥናቱ የትኩረት አቅጣጫ” የተሰኘ መፅሃፍ የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 10 ሰዓት በብሄራዊ ሙዚየም እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ በምረቃ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ የተለያዩ ምሁራን የውይይት ሃሳብ የሚያቀርቡ ሲሆን ምሁራኑ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው፣ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራና አቶ እንዳለ ጌታ ከበደ እንደሆኑ ታውቋል፡፡ የመፅሀፉ ይዘት፡- የፎክሎር ፅንሰሀሳብን በሳይንሳዊ መንገድ ማብራራት፣ በአገራችን የሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ያላቸውን ቃላዊ፣ ቁሳዊና መንፈሳዊ ባህሎችን መሰረት ያደረገ ትንተና መስጠት እና ሌሎችን ያካትታል ተብሏል፡፡ በ335 ገፆች የተዘጋጀው መፅሀፉ፤ በ120 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 2845 times