Monday, 27 July 2015 11:07

ሳምሰንግ የጥገና አገልግሎት የሚሰጥበት ማዕከል ከፈተ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሳምሰንግ ኤሌክትሮኒክስ ለምርቶቹ የጥገና አገልግሎት የሚሰጥበት የደንበኞች አገልግሎት ማዕከል በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከፈተ፡፡
ለሳምሰንግ ሞባይልና ለሁሉም የሳምሰንግ ኤሌክትሮኒክ ምርቶች የጥገና አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል የተባለውንና በአዲስ አበባ ከተማ ቴሌ መድኀኒዓለም አካባቢ የተቋቋመውን የደንበኞች አገልግሎት ማዕከል ከትናንት በስቲያ መርቀው የከፈቱት የኩባንያው የኢትዮጵያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ታዲዮስ አወል ናቸው፡፡ ማዕከሉ ከጥገና በተጨማሪ (Software upgrades, application installation, new devises setup) አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡ አጠቃላይ የማማከር አገልገሎትም ለደንበኞቹ እንደሚሰጥ አቶ ታዲዮስ ተናግረዋል፡፡
ማዕከሉ የዋስትና ፈቃድ ላላቸውም ሆነ ለሌላቸው የሳምሰንግ ምርቶች አገልግሎቱን እንደሚሰጥ የጠቆሙት አቶ ታዲዮስ፤ ደንበኞች ጥራት ባላቸው የመለዋወጫ ዕቃዎች በሙያው በተካኑ ባለሙያዎች የህግና ሌሎች አገልግሎቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገኙ እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡
 እንደፍሪጅ እና የልብስ ማጠቢያ ማሽን ላሉና የትራንስፖርት ወጪን ለሚጠይቁ የሳምሰንግ ምርቶች የማዕከሉ የጥገና ባለሙያዎች ቤት ለቤት በመሄድ አገልግሎቱን እንደሚሰጡና ይህንንም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል፡፡

Read 1583 times