Saturday, 04 July 2015 10:30

የፀሐፍት ጥግ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኑርሁሴን
ሂሮዬ ሺማቡኩሮ
(ስለ ሃያስያን)
- ለማንም ሙገሳም ሆነ ወቀሳ ትኩረት አልሰጥም።
እኔ የምከተለው ስሜቴን ብቻ ነው፡፡
ዎልፍጋንግ አማዴዩስ ሞዛርት
- መፃፍ የሚችሉ ይፅፋሉ፤ መፃፍ የማይችሉ
ይተቻሉ፡፡
ማክስ ሃውቶርን
- አብዛኞቻችን ዘንድ ያለው ችግር በትችት ከመዳን
ይልቅ በሙገሳ መጥፋትን መምረጣችን ነው፡፡
ኖርማን ቪንሰንት ፒል
- ወጣቶች ሞዴሎችን እንጂ ሃያስያንን
አይፈልጉም፡፡
ጆን ውድን
- ሂስ የሚጠይቁ ሰዎች የሚፈልጉት ውዳሴ ብቻ
ነው፡፡
ሶመርሴት ሟም
- ልብህ ትክክል መስሎ የተሰማውን አድርግ፡፡
ትችት እንደሆነ አይቀርልህም፡፡
ኢልኖር ሩስቬልት
- አንድ ሰው ሌሎችን ለማውገዝ ከማሰቡ በፊት
ራሱን ለረዥም ጊዜ መመርመር አለበት፡፡
ሞሌር
- ሃያሲ ስንዝር ከሰጠኸው ተውኔት ልፃፍ ይላል፡፡
ጆን ስቴይንቤክ
- ሂስ የተወለደው ከኪነጥበብ ማህፀን ውስጥ
ነው፡፡
ቻርልስ ባውድሌይር
- ጠንካራ አስተያየቶች የሚሰነዘሩት በሚወዱህ
ሰዎች ብቻ ነው፡፡
ፌዴሪኮ ማዮር
- ሃያሲያን በሥነ ፅሁፍና በሥነ ጥበብ ዘርፍ
ያልተሳካላቸው ሰዎች ናቸው፡፡
ቤንጃሚን ዲስራኤሊ
- አንበሳም ቢሆን ራሱን ከዝንቦች መከላከል
አለበት፡፡
የጀርመናውያን አባባል
- የጎረቤትህን ቤት ብታቃጥል ያንተን ቤት የተሻለ
ገፅታ አያጎናፅፈውም፡፡
ሎ ሆልትዝ
- ሃያስያን ለሚናገሩት ትኩረት አትስጥ፡፡ ለሃያሲ
ክብር ፈፅሞ ሃውልት ቆሞለት አያውቅም፡፡
ዣን ሲቤሊዩስ

Read 1729 times Last modified on Saturday, 04 July 2015 10:34