Saturday, 27 June 2015 09:35

ደራሲና ጋዜጠኛ ሽፈራው መንገሻ በ75 ዓመታቸው አረፉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በቀድሞ አጠራር በሲዳሞ ክ/ሀገር በቡሌ ወረዳ የተወለዱት ደራሲና ጋዜጠኛ ሽፈራው መንገሻ ባደረባቸው ህመም በአገር ውስጥና በውጭ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ባለፈው ሰኔ 12 በ75 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ሲሆን በነጋታው የቀብር ሥነስርዓታቸው በቅዱስ ዮሴፍ ቤ/ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
ለረዥም ዓመታት በተለያዩ የመንግስት መ/ቤቶች ያገለገሉት አቶ ሽፈራው፤ በማስታወቂያ ሚ/ር ፕሬስ መምሪያ የሳምንታዊው “የዛሬይቱ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በመሆን ለብዙ ጊዜያት ማገልገላቸው ተገልጿል፡፡
ደራሲና ጋዜጠኛው የተለያዩ መፃህፍትን ለንባብ ያበቁ ሲሆን ከእነሱም መካከል ታሪክ ጠቀሶቹ “ህግ ያልገዛውን ነፃነት ሃይል ይገዛዋል” እና “የኢትዮጵያ የታሪክ ጉዞ እስከቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ዘመነ መንግስት” የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡
“የኦሾዊት ምስጢር” የተሰኘው የትርጉም ሥራና የፊልም ባለሙያው የበቀለ ወያ ታሪክ የሆነው “የትውልድ አርአያ”ም ከሚታወቁባቸው ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ ደራሲና ጋዜጠኛ ሽፈራው መንገሻ የ3 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

Read 1195 times