Tuesday, 26 May 2015 08:16

አዳነ ግርማ፤ የዋልያዎቹ የአሸናፊነት መንፈስ መቀጠል እንዳለበት መከረ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(3 votes)

 

 

 

አዳነ ግርማ  በብሄራዊ ቡድን 38 ጨዋታዎች በማድረግ 8 ጎሎች አስመዝግቧል

1. ስምንቱ ጎሎች እነዚህ ናቸው

2. በ2008 እኤአ በአዲስ አበባ  በዓለም ዋንጫ ማጣርያ ሞሪታንያ ላይ

3. በ2009 እኤአ በናይሮቢ  በሴካፋ ካፕ ጅቡቲ ላይ

4. በ2011 በአዲስ አበባ ላይ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ማዳጋስካር ላይ

5. በ2011 በዳረሴላም በ2011 ሴካፋ ካፕ በማላዊ ላይ

6. በ2012 በኮተኑ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ቤኒን ላይ

7. በ2012 በካርቱም በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ሱዳን ላይ

8. በ2012 በአዲስ አበባ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ በሱዳን ላይ

9. በ2013 በኔልስፕሪት ደቡብ አፍሪካ በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛምቢያ ላይ

 

               የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ አጥቂ የሆነው አዳነ ግርማ ከዋልያዎቹ አባልነት ጫማ መስቀሉን ባለፈው ሳምንት አስታወቀ፡፡ ከሁለት ዓመታት በፊት የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን  ስብስብ ያሳየው የአሸናፊነት መንፈስ መቀጠል እንዳለበት ለስፖርት አድማስ በሰጠው አስተያየት የመከረው አዳነ፤ ዋልያዎቹ ስኬታማ ለመሆን የሚችሉት በአንድነት  እና በትጋት መስራት ከቻሉ ነው ብሏል፡፡ ከዋልያዎቹ ትውልድ በፊት በነበሩት ብሄራዊ ቡድኖች ስንጫወት ማልያችን አያኮራንም ብሎ ያስታወሰው አዳነ፤ ያኔ ተጨዋቾች በተለያዩ ውዝግቦች እርስ በራስ የሚናናቁ፤ በውጤት ማጣት አንገታቸውን የደፉ ነበሩ ይላል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት ብሄራዊ ቡድኑ በዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተመራበት ወቅት ግን ሁሉ መቀየሩን ይገልፃል፡፡ ዋልያዎቹ በሚል ስሙ የታወቀው ስብስቡ ከሜዳ ውጭ ወሳኝ ጨዋታዎችን በማሸነፍ፤ በአንድነት እና በፍቅር ተከባብሮ በመስራት እንደተሳካላትም በኩራት አንስቷል፡፡ ዋልያዎቹ በተባለው ትውልድ የተገኙ ስኬቶች እና የተፈጠሩ መነቃቃቶች አሁን ላለው ትውልድ ተምሳሌት ሊሆኑ እንደሚገባ የጠቀሰው አዳነ ግርማ ተጨዋቾች ለአገር ክብርና ውጤት ቅድሚያ ሰጥተው በመግባባት መስራታቸውን እጠብቃለሁ ሲል ለስፖርት አድማስ ተናግሯል፡፡ የእግር ኳስ ህይወቱን በክለቡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለመቀጠል እንደሚፈልግና አቅሙ እስካለው ድረስ ለመጫወት ማቀዱን የብሄራዊ ቡድን ጫማውን በሰቀለበት ወቅት የተናገረው አዳነ፤ ጎን ለጎን ወደ ኢንቨስትመንት መግባቱ እየተገለፀም ነው፡፡

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ተጨዋቾች ታሪክ ፈርቀዳጅ በሆነ መንገድ እስከ  4.5 ሚሊዮን ብር ወጭ በማድረግ በሃዋሳ ልዩ መዝናኛ ሆቴል ገንብቷል፡፡ ወደ ቢዝነሱ መግባቱ በእግር ኳስ ህይወቱ ላይ ምንም አይነት ጫና እንደማይፈጥርበትም ተናግሯል፡፡

አዳነ ግርማ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ተከታታይ አመታት ለሀዋሳ ከነማ ክለብ የተጫወተ ሲሆን፤ ከዚህ የትውልድ ከተማው ክለብ ጋር ሁለት የፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮና እንዲሁም አንድ የጥሎ ማለፍ በድምሩ  ዋንጫዎችን  ተቀዳጅቷል፡፡   ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ  ደግሞ  ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ላለፉት 8 የውድድር ዘመናት ሲጫወት የቆየሲሆን ለ6 ጊዜያት የፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮናነት ክብሮችን እንዲሁም በጥሎ ማለፍ እና በአሸናፊዎች አሸናፊ ሌሎች ዋንጫዎችንም ተጎናፅፏል፡፡ በክለብ ደረጃ ለሃዋሳ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሲጫወት ባለፉት 10 የውድድር ዘመናት በተለያዩ ውድድሮች ከ100 በላይ ጎሎችንም በስሙ ማስመዝገቡ ይገመታል፡፡

አዳነ ግርማ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ለስምንት ዓመታት በብሄራዊ ቡድኑ ተጫውቷል፡፡ በተለይም ከ31 አመት በኋላ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በ2013ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደነበረው ይታወሳል፡፡ በዚሁ ደቡብ አፍሪካው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አዳነ ግርማ ከ37 ዓመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የተመዘገበችውን ብቸኛ ግብ ያስቆጠረውም እሱ ነው፡፡ በ2014 መግቢያ ላይ በዚያው ደቡብ አፍሪካ በተደረገው 3ኛው የቻን ውድድር እንዲሁም በዓለም ዋንጫ ማጣርያ እስከመጨረሻው ማጣርያ በተደረገው ትንቅንቅ ላይም ዋልያዎቹን በማል ሞተርነትና በአምበልነት በመምራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ነበረው፡፡ አዳነ ግርማ በተጨዋችነትዘመኑ መሰለፍ ያልቻለው በግብ ጠባቂነት ስፍራ ብቻ ነው፡፡ አጥቂ፣ አማካይ፣ የመስመር ተመላላሽ ፤የመስመር ተከላካይ፣ መሃል ተከላካይ ሆኖ  በመጫወት ሁለገብ ብቃቱን አሳይቷል፡፡

ከ2 ዓመት በፊት በነበረው የዋልያዎቹ ስኬት አዳነ ግርማ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ትኩረት ያገኘባቸው ሁኔታዎች ነበሩ፡፡ በወቅቱ ነዋሪነታቸውን በዱባይ ያደረጉ አምስት ኢትዮጵያዊያን ጓደኛሞች በአፍሪካ ዋንጫላይ ባገባት ጎል ተደንቀው እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ሺ ዶላር በማዋጣት በ10ሺ ዶላር  ቶዮታ ኮሎራ ሸልመውታል፡፡ የዋልያዎቹ አፍሪካ ዋንጫው ተሳትፎ ከተጠናቀቀ በኋላ  ደግሞ በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተዘጋጅቶ በነበረው የእራት ግብዣ ለብሶት የነበረው 19 ቁጥር ማሊያ 93,000 ራንድ እስከ 162ሺ ብር ተጫርቷል፡፡

አዳነ ግርማ  በብሄራዊ ቡድን 38 ጨዋታዎች በማድረግ 8 ጎሎች አስመዝግቧል

1. ስምንቱ ጎሎች እነዚህ ናቸው

2. በ2008 እኤአ በአዲስ አበባ  በዓለም ዋንጫ ማጣርያ ሞሪታንያ ላይ

3. በ2009 እኤአ በናይሮቢ  በሴካፋ ካፕ ጅቡቲ ላይ

4. በ2011 በአዲስ አበባ ላይ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ማዳጋስካር ላይ

5. በ2011 በዳረሴላም በ2011 ሴካፋ ካፕ በማላዊ ላይ

6. በ2012 በኮተኑ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ቤኒን ላይ

7. በ2012 በካርቱም በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ሱዳን ላይ

8. በ2012 በአዲስ አበባ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ በሱዳን ላይ

9. በ2013 በኔልስፕሪት ደቡብ አፍሪካ በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛምቢያ ላይ

 

               የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ አጥቂ የሆነው አዳነ ግርማ ከዋልያዎቹ አባልነት ጫማ መስቀሉን ባለፈው ሳምንት አስታወቀ፡፡ ከሁለት ዓመታት በፊት የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን  ስብስብ ያሳየው የአሸናፊነት መንፈስ መቀጠል እንዳለበት ለስፖርት አድማስ በሰጠው አስተያየት የመከረው አዳነ፤ ዋልያዎቹ ስኬታማ ለመሆን የሚችሉት በአንድነት  እና በትጋት መስራት ከቻሉ ነው ብሏል፡፡ ከዋልያዎቹ ትውልድ በፊት በነበሩት ብሄራዊ ቡድኖች ስንጫወት ማልያችን አያኮራንም ብሎ ያስታወሰው አዳነ፤ ያኔ ተጨዋቾች በተለያዩ ውዝግቦች እርስ በራስ የሚናናቁ፤ በውጤት ማጣት አንገታቸውን የደፉ ነበሩ ይላል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት ብሄራዊ ቡድኑ በዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተመራበት ወቅት ግን ሁሉ መቀየሩን ይገልፃል፡፡ ዋልያዎቹ በሚል ስሙ የታወቀው ስብስቡ ከሜዳ ውጭ ወሳኝ ጨዋታዎችን በማሸነፍ፤ በአንድነት እና በፍቅር ተከባብሮ በመስራት እንደተሳካላትም በኩራት አንስቷል፡፡ ዋልያዎቹ በተባለው ትውልድ የተገኙ ስኬቶች እና የተፈጠሩ መነቃቃቶች አሁን ላለው ትውልድ ተምሳሌት ሊሆኑ እንደሚገባ የጠቀሰው አዳነ ግርማ ተጨዋቾች ለአገር ክብርና ውጤት ቅድሚያ ሰጥተው በመግባባት መስራታቸውን እጠብቃለሁ ሲል ለስፖርት አድማስ ተናግሯል፡፡ የእግር ኳስ ህይወቱን በክለቡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለመቀጠል እንደሚፈልግና አቅሙ እስካለው ድረስ ለመጫወት ማቀዱን የብሄራዊ ቡድን ጫማውን በሰቀለበት ወቅት የተናገረው አዳነ፤ ጎን ለጎን ወደ ኢንቨስትመንት መግባቱ እየተገለፀም ነው፡፡

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ተጨዋቾች ታሪክ ፈርቀዳጅ በሆነ መንገድ እስከ  4.5 ሚሊዮን ብር ወጭ በማድረግ በሃዋሳ ልዩ መዝናኛ ሆቴል ገንብቷል፡፡ ወደ ቢዝነሱ መግባቱ በእግር ኳስ ህይወቱ ላይ ምንም አይነት ጫና እንደማይፈጥርበትም ተናግሯል፡፡

አዳነ ግርማ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ተከታታይ አመታት ለሀዋሳ ከነማ ክለብ የተጫወተ ሲሆን፤ ከዚህ የትውልድ ከተማው ክለብ ጋር ሁለት የፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮና እንዲሁም አንድ የጥሎ ማለፍ በድምሩ  ዋንጫዎችን  ተቀዳጅቷል፡፡   ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ  ደግሞ  ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ላለፉት 8 የውድድር ዘመናት ሲጫወት የቆየሲሆን ለ6 ጊዜያት የፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮናነት ክብሮችን እንዲሁም በጥሎ ማለፍ እና በአሸናፊዎች አሸናፊ ሌሎች ዋንጫዎችንም ተጎናፅፏል፡፡ በክለብ ደረጃ ለሃዋሳ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሲጫወት ባለፉት 10 የውድድር ዘመናት በተለያዩ ውድድሮች ከ100 በላይ ጎሎችንም በስሙ ማስመዝገቡ ይገመታል፡፡

አዳነ ግርማ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ለስምንት ዓመታት በብሄራዊ ቡድኑ ተጫውቷል፡፡ በተለይም ከ31 አመት በኋላ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በ2013ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደነበረው ይታወሳል፡፡ በዚሁ ደቡብ አፍሪካው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አዳነ ግርማ ከ37 ዓመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የተመዘገበችውን ብቸኛ ግብ ያስቆጠረውም እሱ ነው፡፡ በ2014 መግቢያ ላይ በዚያው ደቡብ አፍሪካ በተደረገው 3ኛው የቻን ውድድር እንዲሁም በዓለም ዋንጫ ማጣርያ እስከመጨረሻው ማጣርያ በተደረገው ትንቅንቅ ላይም ዋልያዎቹን በማል ሞተርነትና በአምበልነት በመምራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ነበረው፡፡ አዳነ ግርማ በተጨዋችነትዘመኑ መሰለፍ ያልቻለው በግብ ጠባቂነት ስፍራ ብቻ ነው፡፡ አጥቂ፣ አማካይ፣ የመስመር ተመላላሽ ፤የመስመር ተከላካይ፣ መሃል ተከላካይ ሆኖ  በመጫወት ሁለገብ ብቃቱን አሳይቷል፡፡

ከ2 ዓመት በፊት በነበረው የዋልያዎቹ ስኬት አዳነ ግርማ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ትኩረት ያገኘባቸው ሁኔታዎች ነበሩ፡፡ በወቅቱ ነዋሪነታቸውን በዱባይ ያደረጉ አምስት ኢትዮጵያዊያን ጓደኛሞች በአፍሪካ ዋንጫላይ ባገባት ጎል ተደንቀው እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ሺ ዶላር በማዋጣት በ10ሺ ዶላር  ቶዮታ ኮሎራ ሸልመውታል፡፡ የዋልያዎቹ አፍሪካ ዋንጫው ተሳትፎ ከተጠናቀቀ በኋላ  ደግሞ በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተዘጋጅቶ በነበረው የእራት ግብዣ ለብሶት የነበረው 19 ቁጥር ማሊያ 93,000 ራንድ እስከ 162ሺ ብር ተጫርቷል፡፡

 

 

 

Read 3903 times