Tuesday, 26 May 2015 08:11

የዋልያዎቹ ዝግጅት በአስቸኳይ መጀመር አለበት

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(1 Vote)

 

 

 

ሌሶቶ እና ሲሸልስ በኮሳፋ ካፕ ተሟሙቀዋል

         አልጄርያ እስከ ኢትዮጵያ ግጥሚያ የወዳጅነት ጨዋታ  የላትም

         ኬንያ የቻን ማጣርያን በሜዳዋ ለመጨረስ ዝግጅቷ ቀጥሏል

                                        ከወር በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ እና በቻን ውድድር የማጣርያ ጨዋታዎች የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአስቸኳይ ዝግጅቱን መስራት እንዳለበት ሁኔታዎች እያመለከቱ ነው፡፡ የዋልያዎቹ ዋና አሰልጣኝ  ሆኖ እንዲሰራ በእግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተመረጠው  ዮሐንስ ሳህሌ ከ2 ሳምንት በፊት  ስራውን በይፋ  የጀመረ ቢሆንም ብሄራዊ ቡድኑ እስካሁን አልተሰባሰበም፡፡ ከአሰልጣኙ ጋር በሃላፊነቱ ዙርያ የተካሄዱት ተከታታይ ውይይቶች በተሳካ ሁኔታ መደረጋቸውን የገለፀው ፌደሬሽኑ፤ ለብሄራዊ ቡድን የሚያስፈልጉ የተለያዩ ትኩረቶችእና የወዳጅነት ጨዋታዎችን አስመልክቶ ብዙም ተጨባጭ ነገሮችን አላሳወቀም፡፡

በፌደሬሽኑ እና በዮሃንስ ሳህሌ የውል ስምምነት መሰረት በ2017 እኤአ ጋቦን በምታስተናግደው የአፍሪካ ዋንጫ  ዋሊያዎቹ በተደለደሉበት ምድብ 10 በሚያደርጓቸው ስድስት የማጣሪያ ጨዋታዎች ወደ ዋናው ውድደድር ለማለፍ የሚያስላቸውን  ነጥብ ማስመዝገብ እና  በ31ኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ  ተሳታፊነታቸውን የማረጋጋጥ ሃላፊነት ተጥሏል፡፡ በቻን 2016 እና በሴካፋ አህጉራዊና ክፍለ አህጉራዊ  ውድድሮችም አመርቂ ውጤት እንደሚጠበቅባቸው ተማምነዋል፡፡ አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ለ31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ካበቁ የስራ ዘመናቸው እስከ ኤፕሪል 2017 ዓ.ም ድረስ እንደጸና ይቆያል ተብሏል፡፡  ፌዴሬሽኑ ለአሰልጣኝ ዮሐንስ  75ሺ ብር  ወርሃዊ ደመወዝ ለመክፈል የተስማማ ሲሆን ተሽከርካሪ ከሾፌር ጋር እንዲሁም ባለመስመር የሞባይል ስልክና የጤና ኢንሹራንስ ከማሟላት በተጨማሪም  ውጤትን መሰረት ያደረገ ማበረታቻ  እንደሚኖር አስታውቋል፡፡

ዋና አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ የሚመራው ለአፍሪካ  ዋንጫ እና  ለቻን የማጣሪያ ጨዋታዎች ዝግጅት ለመጀመር ግንቦት 24  ተጫዋቾች በሆቴል እንዲሰባሰቡ ከሳምንት በፊት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ለመጀመሪያ ዙር ምርጫ  44 ተጫዋቾች ጥሪ እንደሚቀርብላቸው ሲገለጽ ስም ዝርዝራቸው ልምምድ ከመጀመሩ ከአንድ ሳምንት በፊት ይፋ እንደሚደረግ፤  ከጥቂት ቀናት ልምምድ በኋላም ከውጭ ሀገር ክለቦች የሚጠሩትን 4 ወይም 5 ተጫዋቾች ጨምሮ  25 ተጫዋቾች  በሁለተኛ ዙር ምርጫ ተለይተው ለወዳጅነት እና ከሌሴቶ ጋር ለሚካሄደው ወሳኝ የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመርያ ማጣሪያ ጨዋታ ልምምዳቸውን እንደሚቀጥሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በ30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎችና በሌሎች አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች የተገኘውን ልምድና ያጋጠሙ የአሠራር ችግሮችን  በማጤን ለብሔራዊ ቡድኑ ውጤታማነትና ተወዳዳሪነት ከፍተኛ እገዛ ለማድረግ በፌደሬሽኑ በኩል እቅድ መኖሩን ቡድን መሪው አቶ ዮሴፍ ተናግረዋል፡፡ በዚሁ መሠረት የትጥቅ ፣ የሆቴል፣ የልምምድ ሜዳ፣ የመረጃ ልውውጥ፣ የአውሮኘላን ትኬትና የጉዞ ሰነዶችን አስቀድሞ የማዘጋጀትና እንዲሁም የወዳጅነት ጨዋታ ቅድመ ዝግጅት እና አጠቃላይ የጊዜ ሰሌዳ የመቅረፅና የማስፈፀም ሥራዎች በተጠና እና በተቀናጀ የአሠራር አግባብ ተግባራዊ እንደሚሆንም ተገልጿል፡፡ ከውድድር፣ ከዳኝነት፣ ከህክምና ፣ከሥልጠና ቡድን አባላት ጋር የሚኖረውን የሥራ ግንኙነትና ከፌዴሬሽኑ የሚጠበቀውን ሙያዊና አስተዳደራዊ ድጋፍ በተመለከተም ኃላፊነትና ተጠያቂነትን በአገናዘበ መልኩ የዝግጅት መርሀ ግብሩ እንደሚተገበር ታውቋል፡፡  የብሔራዊ ቡድኑ አሠልጣኝ በተሰጣቸው የሥራ ኃላፊነት መሠረት ለብሔራዊ ቡድን በረዳት አሠልጣኝነት እና በግብ ጠባቂ አሰልጣኝነት የመረጧቸው ፋሲል ተካልኝ እና ዓሊ ረዲን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሰኔ ወር የሚያካሂዳቸው ጨዋታዎች የሚያስተናግዱባቸውን ስታዲየሞች በተመለከተም ከአየር ሁኔታ ትንበያና የተጋጣሚዎችን አጠቃላይ ሁኔታ መሠረት አድርጎ ሰሞኑን ውሳኔ እንደሚሰጥበት ይጠበቃል፡፡

ሌሶቶ እና   ሲሸልስ በኮሳፋ ካፕ ተሟሙቀዋል

ለ31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሚደረግ የማጣርያ ውድድር ላይ በምድብ 10 የኢትዮጵያ ተጋጣሚዎች የሆኑት ሌሶቶ እና ሲሸልስ በ15ኛው የኮሳፋ ካፕ ላይ በመሳተፍ ዝግጅታቸውን በተጠናከረ ሁኔታ ጀምረዋል። በወርሃዊው የፊፋ የእግር ኳስ ደረጃቸው 127ኛ እና 187ኛ ላይ እንደቅደምተከተላቸው የሚገኙት ሌሶቶ እና ሲሸልስ ምንም እንኳን ከኢትዮጵያ በታች ቢሆኑም በማጣርያው አስፈላጊውን እድገት እና መነቃቃት ለመፍጠር ትኩረት አድርገዋል፡፡ በደቡብ አፍሪካ እግር ኳስ አገራት ሻምፒዮና ላይ ተሳትፎ ያደረጉት ሁለቱ ብሄራዊ ቡድኖች በቀጣይ በአፍሪካ ዋንጫ እና በቻን የማጣርያ ጨዋታዎች ለሚያደርጉት ዝግጅት የውድድር መድረኩን እንደመሟሟቂያ እንደተጠቀሙበት ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡ የሌሶቶ ብሄራዊ ቡድን በኮሳፋ ካፕ በምድብ 2 ከማዳጋስካር፤ ከስዋዚላንድ እና ከታንዛኒያ ጋር ተደልድሎ ተጫውቷል፡፡ ኮሳፋ ካፕ ከመጀመሩ በፊት የሌሶቶ ብሄራዊ ቡድን ከደቡብ አፍሪካ አቻው ጋር የአቋም መፈተሻ ግጥሚያውን በሩስተንበርግ አድርጎ 0ለ0 አቻ ተለያይቶ ነበር፡፡ የደቡብ አፍሪካው ሚዲያዎች ግን ከሌሶቶ ጋር የተደረገው የወዳጅነት ጨዋታ በፊፋ እውቅና የማይኖረው እና ወርሃዊው የእግር ኳስ ደረጃ ምንም ነጥብ የማያሰጥ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

ባለፈው ቅዳሜ ደግሞ በምድብ የመጀመርያው ጨዋታቸው ከማዳጋስካር ተገናኝቶ  2ለ1 የተሸነፈ ሲሆን በሁለተኛ የምድብ ጨዋታቸው ረቡእ እለት ከስዋዚላንድ ተጋጥመው በድጋሚ 2ለ0 ተሸንፏል፡፡ በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታውትናንት በውድድሩ ላይ ተጋባዥ ከነበረችው የምስራቅ አፍሪካዋ አገር ታንዛኒያ ጋር ያደረገው ነው፡፡ ይሄው ግጥሚያ በተለይ የሌሶቶ ቡድን ከኢትዮጵያ ጋር ለሚያደረገው የምድብ የመጀመርያ ጨዋታ ከፍተኛ ልምድ እንደሚገኝበት ለመረዳት ይቻላል። በኮሳፋ ካፕ የተሳተፈው የሌሶቶ ቡድን በወጣቶች እንደተገነባ ለሱፕርስፖርት የገለፁት አሰልጣኙ ሴፋኒ ማቴቴ፤ ቡድናቸው በአፍሪካ ሀ 20 ሻምፒዮንሺፕ በተሳተፉ 6 ወጣት ተጨዋቾች የተገነባ እንደሆነና በኮሳፋ ጥሩ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚያጠናክራቸው ተናግረዋል፡፡ የሌሶቶ እግር ኳስ ፌደሬሽን ሃላፊዎች ብሄራዊ ቡድናቸው በኮሳፋ ሲሳተፍ እስከፍፃሜ ለመድረስ አቅዶ መሆኑን ተናግረው ነበር፡፡

በሌላ በኩል በምድብ 1 ከደቡብ አፍሪካ፤ ዚምባቡዌ እና ናሚቢያ ጋር የተደለደለው የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን፤ ጥሩ አጀማመር አሳይቶ ነበር፡፡ በምድቡ የመጀመርያ ጨዋታ ከናሚቢያ ጋር 0ለ0 አቻ ተለያየና በምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ ባለፈው ማክሰኞ ከዚምባቡዌ ጋር ተጋጥሞ ግን 1ለ0 በመሸነፉ ግን ከውድድሩ ውጭ ሆኗል፡፡ በምድባቸው የመጨረሻ ጨዋታቸውን ከምትመጣጠናቸው ሞውሪሽዬስ ጋር ያደረጉት ለክብር ብቻ ነው፡፡ ዋና አሰልጣኙ ኡልሪች ማቲዮት ቡድናቸው በኮሳፋ ካፕ ሲሳተፍ በምድቡ በከፍተኛ የእግር ኳስ ደረጃ ላይ የሚገኙ ቡድኖችን ቢገጥምም ዋና ዓላማቸው በየትኛው ቡድን ላለመሸነፍ ነው ብለዋል፡፡ የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን በደቡብ አፍሪካ ላላፉት 2 ሳምንታት ተቀምጦ ጠንካራ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነበር፡፡ ማቲዩት በተጨማሪ አስተያየታቸው በቡድናቸው የኮሳፋ ካፕ ተሳትፎ አንዳንድ ተጨዋቾች በደቡብ አፍሪካ ክለቦች የሚገቡበትን እድል ከመፍጠሩም በላይ በቀጣይ በሚሳተፉባቸው አህጉራዊ የማጣርያ ውድድሮች የተሰጠውን ዝቅ ያለ ግምት ለማስተካከል ምቹ መድረክ ይፈጥርልናል ብለዋል፡፡ ሲሸልስ ከኮሳፋ ካፕ የምድብ ጨዋታዎች መሰናበቷ ብዙም የማያስቆጭ እንደነበር የገለፁት ዋና አሰልጣኙ ኡልሪች ማቲዮት፤ ባለፉት አመታት በሻምፒዮናው ሲሳተፉ በሁለት ጨዋታዎች እስከ ስምንት ጎሎች እንደተቆጠረባቸው አስታውሰው ዘንድሮ ግን አንድ ጎል ብቻ እንደተመዘገበበባቸው እና በመከላከል ረገድ ጥሩ ለውጥ ማየታቸው ተስፋ እንዳሳደረባቸው ተናግረዋል፡፡ የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን በነሐሴ ወር በህንድ ውቅያኖስ ዙርያ በሚገኙ ደሴቶች እና አገራት መካከል በሚደረግ ሻምፒዮናም ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡

አልጄርያ እስከ ኢትዮጵያ ግጥሚያ የወዳጅነት ጨዋታ  የላትም

የአልጄርያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት ፈረንሳዊው ክርስትያን ጉርኩፍ በምድባቸው ጠንካራ ተፎካካሪያቸው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን መሆኑን በተደጋጋሚ እየገለፁ ናቸው፡፡ ምድብ 10 ለአልጄርያ ቀላል ነው መባሉን በፍፁም አልቀበልም የሚሉት ጉርኩፍ፤ ለኢትዮጵያ ቡድን የተለየ ትኩረት ቢኖረንም ሌሶቶ እና ሲሸልስንም በቅርበት እንከታተላለን ይላሉ፡፡ ይህን አቋማቸውን በተግባር ለማሳየትም ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው የኮሳፋ ካፕን እየተመለከቱ ናቸው፡፡ በአልጄርያ ሊግ የሚገኙ ምርጥ ተጨዋቾችን በቡድናቸው ስብስብ ለማካተት ከፍተኛ ክትትል እያደረጉ ያሉት አሰልጣኙ ፕሮፌሽናሎቻቸውንም በሁሉም የምድብ ማጣርያዎች በተገቢው ጊዜ አሰባስበው ለመጠቀም እየሰሩ ናቸው፡፡

ለክርስትያን ጉርክፍ ዝግጅት ብቸኛዎቹ እንቅፋቶች በአውሮፓ ክለቦች የሚጫወቱ ተጨዋቾችን ለመሰብሰብ የሚፈጠሩ ውስብስብ ሁኔታዎች እና በተለይ በፊፋ የወዳጅነት ጨዋታዎች መርሃ ግብር መሰረት በመጀመርያዎቹ የምድብ ማጣርያ ሶስት ጨዋታዎች ለሚቀጥሉት ሶስት እና አራት ወራት ተጋጣሚ እንደሌላቸው መገንዘባቸው ነው ተብሏል፡፡ አንዳንድ የአልጄርያ ሚዲያዎች እንደገለፁት አረንጓዴዎቹ 2016 እኤአ እስኪገባ የወዳጅነት ጨዋታ የማያገኙ ሲሆን ምናልባት ግን በአዲሱ የፈረንጆች አመት ዋዜማ ከአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮና ኮትዲቯር ጋር የመያገናኛቸው የፊፋ የወዳጅነት ጨዋታ መርሃ ግብር የመጠቀም እድል እንዳላቸው አመልክተዋል፡፡

ኬንያ የቻን ማጣርያን በሜዳዋ ለመጨረስ ዝግጅቷ ቀጥሏል

በሩዋንዳ አዘጋጅነት በ2016 እኤአ ላይ ለሚደረገው 4ኛው የቻን ውድድር የሚደረገውን የመጀመርያ ጨዋታን ኬንያ በሜዳዋ በማስተናገዷ ደስተኛ እንደሆነች ዘገባዎች እያመለከቱ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያን ጠንካራ ተፎካካሪነት በሜዳቸው በሚያስመዘግቡት ውጤት በመጨረስ ለመልሱ ለመዘጋጀት እቅድ እንዳላቸው የገለፁት ዋና አሰልጣኙ ቦቢ ዊልያምሰን ለዝግጅታቸው ምንም አይነት እንቅፋት መኖር እንደሌለበት እያሳሰቡ ናቸው፡፡ የኬንያ ፕሪሚዬር ሊግ አስተዳዳሪዎች ለብሄራዊ ቡድን በሚለቀቁ ተጨዋቾች ዙርያ ሰሞኑን ያወጡት አዲስ ደንብ ይህን ማሳሰቢያቸውን ያከበረ አይደለም በሚል ተተችቷል፡፡ የፕሪሚዬር ሊጉ ክለቦች ተጨዋቾቻቸውን ለመልቀቅ ቅድመ መስፈርት ማቅረባቸው ከፌደሬሽኑ እና ከሃራምቤ ኮከቦች አሰልጣኝ ጋር ማጋጨት ጀምሯል። የአገሪቱ ክለቦች ለወዳጅነት ጨዋታ  ተጨዋቾቻቸውን የሚለቁት ግጥሚያው 2 ቀን ሲቀረው እንዲሆንና ለአህጉራዊ ውድድር ደግሞ ግጥሚያው 4 እና 5 ቀናት ሲቀረው ተስማምተዋል ተብሏል፡፡

የኬንያ ብሄራዊ ቡድን ስታርታይምስ በተባለ የቻይና ኩባንያ በ270 ሚሊዮን የኬንያ ሽልንግ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ስፖንሰር ተደርጓል፡፡

ሌሶቶ እና ሲሸልስ በኮሳፋ ካፕ ተሟሙቀዋል

         አልጄርያ እስከ ኢትዮጵያ ግጥሚያ የወዳጅነት ጨዋታ  የላትም

         ኬንያ የቻን ማጣርያን በሜዳዋ ለመጨረስ ዝግጅቷ ቀጥሏል

                                        ከወር በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ እና በቻን ውድድር የማጣርያ ጨዋታዎች የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአስቸኳይ ዝግጅቱን መስራት እንዳለበት ሁኔታዎች እያመለከቱ ነው፡፡ የዋልያዎቹ ዋና አሰልጣኝ  ሆኖ እንዲሰራ በእግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተመረጠው  ዮሐንስ ሳህሌ ከ2 ሳምንት በፊት  ስራውን በይፋ  የጀመረ ቢሆንም ብሄራዊ ቡድኑ እስካሁን አልተሰባሰበም፡፡ ከአሰልጣኙ ጋር በሃላፊነቱ ዙርያ የተካሄዱት ተከታታይ ውይይቶች በተሳካ ሁኔታ መደረጋቸውን የገለፀው ፌደሬሽኑ፤ ለብሄራዊ ቡድን የሚያስፈልጉ የተለያዩ ትኩረቶችእና የወዳጅነት ጨዋታዎችን አስመልክቶ ብዙም ተጨባጭ ነገሮችን አላሳወቀም፡፡

በፌደሬሽኑ እና በዮሃንስ ሳህሌ የውል ስምምነት መሰረት በ2017 እኤአ ጋቦን በምታስተናግደው የአፍሪካ ዋንጫ  ዋሊያዎቹ በተደለደሉበት ምድብ 10 በሚያደርጓቸው ስድስት የማጣሪያ ጨዋታዎች ወደ ዋናው ውድደድር ለማለፍ የሚያስላቸውን  ነጥብ ማስመዝገብ እና  በ31ኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ  ተሳታፊነታቸውን የማረጋጋጥ ሃላፊነት ተጥሏል፡፡ በቻን 2016 እና በሴካፋ አህጉራዊና ክፍለ አህጉራዊ  ውድድሮችም አመርቂ ውጤት እንደሚጠበቅባቸው ተማምነዋል፡፡ አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ለ31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ካበቁ የስራ ዘመናቸው እስከ ኤፕሪል 2017 ዓ.ም ድረስ እንደጸና ይቆያል ተብሏል፡፡  ፌዴሬሽኑ ለአሰልጣኝ ዮሐንስ  75ሺ ብር  ወርሃዊ ደመወዝ ለመክፈል የተስማማ ሲሆን ተሽከርካሪ ከሾፌር ጋር እንዲሁም ባለመስመር የሞባይል ስልክና የጤና ኢንሹራንስ ከማሟላት በተጨማሪም  ውጤትን መሰረት ያደረገ ማበረታቻ  እንደሚኖር አስታውቋል፡፡

ዋና አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ የሚመራው ለአፍሪካ  ዋንጫ እና  ለቻን የማጣሪያ ጨዋታዎች ዝግጅት ለመጀመር ግንቦት 24  ተጫዋቾች በሆቴል እንዲሰባሰቡ ከሳምንት በፊት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ለመጀመሪያ ዙር ምርጫ  44 ተጫዋቾች ጥሪ እንደሚቀርብላቸው ሲገለጽ ስም ዝርዝራቸው ልምምድ ከመጀመሩ ከአንድ ሳምንት በፊት ይፋ እንደሚደረግ፤  ከጥቂት ቀናት ልምምድ በኋላም ከውጭ ሀገር ክለቦች የሚጠሩትን 4 ወይም 5 ተጫዋቾች ጨምሮ  25 ተጫዋቾች  በሁለተኛ ዙር ምርጫ ተለይተው ለወዳጅነት እና ከሌሴቶ ጋር ለሚካሄደው ወሳኝ የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመርያ ማጣሪያ ጨዋታ ልምምዳቸውን እንደሚቀጥሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በ30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎችና በሌሎች አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች የተገኘውን ልምድና ያጋጠሙ የአሠራር ችግሮችን  በማጤን ለብሔራዊ ቡድኑ ውጤታማነትና ተወዳዳሪነት ከፍተኛ እገዛ ለማድረግ በፌደሬሽኑ በኩል እቅድ መኖሩን ቡድን መሪው አቶ ዮሴፍ ተናግረዋል፡፡ በዚሁ መሠረት የትጥቅ ፣ የሆቴል፣ የልምምድ ሜዳ፣ የመረጃ ልውውጥ፣ የአውሮኘላን ትኬትና የጉዞ ሰነዶችን አስቀድሞ የማዘጋጀትና እንዲሁም የወዳጅነት ጨዋታ ቅድመ ዝግጅት እና አጠቃላይ የጊዜ ሰሌዳ የመቅረፅና የማስፈፀም ሥራዎች በተጠና እና በተቀናጀ የአሠራር አግባብ ተግባራዊ እንደሚሆንም ተገልጿል፡፡ ከውድድር፣ ከዳኝነት፣ ከህክምና ፣ከሥልጠና ቡድን አባላት ጋር የሚኖረውን የሥራ ግንኙነትና ከፌዴሬሽኑ የሚጠበቀውን ሙያዊና አስተዳደራዊ ድጋፍ በተመለከተም ኃላፊነትና ተጠያቂነትን በአገናዘበ መልኩ የዝግጅት መርሀ ግብሩ እንደሚተገበር ታውቋል፡፡  የብሔራዊ ቡድኑ አሠልጣኝ በተሰጣቸው የሥራ ኃላፊነት መሠረት ለብሔራዊ ቡድን በረዳት አሠልጣኝነት እና በግብ ጠባቂ አሰልጣኝነት የመረጧቸው ፋሲል ተካልኝ እና ዓሊ ረዲን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሰኔ ወር የሚያካሂዳቸው ጨዋታዎች የሚያስተናግዱባቸውን ስታዲየሞች በተመለከተም ከአየር ሁኔታ ትንበያና የተጋጣሚዎችን አጠቃላይ ሁኔታ መሠረት አድርጎ ሰሞኑን ውሳኔ እንደሚሰጥበት ይጠበቃል፡፡

ሌሶቶ እና   ሲሸልስ በኮሳፋ ካፕ ተሟሙቀዋል

ለ31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሚደረግ የማጣርያ ውድድር ላይ በምድብ 10 የኢትዮጵያ ተጋጣሚዎች የሆኑት ሌሶቶ እና ሲሸልስ በ15ኛው የኮሳፋ ካፕ ላይ በመሳተፍ ዝግጅታቸውን በተጠናከረ ሁኔታ ጀምረዋል። በወርሃዊው የፊፋ የእግር ኳስ ደረጃቸው 127ኛ እና 187ኛ ላይ እንደቅደምተከተላቸው የሚገኙት ሌሶቶ እና ሲሸልስ ምንም እንኳን ከኢትዮጵያ በታች ቢሆኑም በማጣርያው አስፈላጊውን እድገት እና መነቃቃት ለመፍጠር ትኩረት አድርገዋል፡፡ በደቡብ አፍሪካ እግር ኳስ አገራት ሻምፒዮና ላይ ተሳትፎ ያደረጉት ሁለቱ ብሄራዊ ቡድኖች በቀጣይ በአፍሪካ ዋንጫ እና በቻን የማጣርያ ጨዋታዎች ለሚያደርጉት ዝግጅት የውድድር መድረኩን እንደመሟሟቂያ እንደተጠቀሙበት ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡ የሌሶቶ ብሄራዊ ቡድን በኮሳፋ ካፕ በምድብ 2 ከማዳጋስካር፤ ከስዋዚላንድ እና ከታንዛኒያ ጋር ተደልድሎ ተጫውቷል፡፡ ኮሳፋ ካፕ ከመጀመሩ በፊት የሌሶቶ ብሄራዊ ቡድን ከደቡብ አፍሪካ አቻው ጋር የአቋም መፈተሻ ግጥሚያውን በሩስተንበርግ አድርጎ 0ለ0 አቻ ተለያይቶ ነበር፡፡ የደቡብ አፍሪካው ሚዲያዎች ግን ከሌሶቶ ጋር የተደረገው የወዳጅነት ጨዋታ በፊፋ እውቅና የማይኖረው እና ወርሃዊው የእግር ኳስ ደረጃ ምንም ነጥብ የማያሰጥ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

ባለፈው ቅዳሜ ደግሞ በምድብ የመጀመርያው ጨዋታቸው ከማዳጋስካር ተገናኝቶ  2ለ1 የተሸነፈ ሲሆን በሁለተኛ የምድብ ጨዋታቸው ረቡእ እለት ከስዋዚላንድ ተጋጥመው በድጋሚ 2ለ0 ተሸንፏል፡፡ በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታውትናንት በውድድሩ ላይ ተጋባዥ ከነበረችው የምስራቅ አፍሪካዋ አገር ታንዛኒያ ጋር ያደረገው ነው፡፡ ይሄው ግጥሚያ በተለይ የሌሶቶ ቡድን ከኢትዮጵያ ጋር ለሚያደረገው የምድብ የመጀመርያ ጨዋታ ከፍተኛ ልምድ እንደሚገኝበት ለመረዳት ይቻላል። በኮሳፋ ካፕ የተሳተፈው የሌሶቶ ቡድን በወጣቶች እንደተገነባ ለሱፕርስፖርት የገለፁት አሰልጣኙ ሴፋኒ ማቴቴ፤ ቡድናቸው በአፍሪካ ሀ 20 ሻምፒዮንሺፕ በተሳተፉ 6 ወጣት ተጨዋቾች የተገነባ እንደሆነና በኮሳፋ ጥሩ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚያጠናክራቸው ተናግረዋል፡፡ የሌሶቶ እግር ኳስ ፌደሬሽን ሃላፊዎች ብሄራዊ ቡድናቸው በኮሳፋ ሲሳተፍ እስከፍፃሜ ለመድረስ አቅዶ መሆኑን ተናግረው ነበር፡፡

በሌላ በኩል በምድብ 1 ከደቡብ አፍሪካ፤ ዚምባቡዌ እና ናሚቢያ ጋር የተደለደለው የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን፤ ጥሩ አጀማመር አሳይቶ ነበር፡፡ በምድቡ የመጀመርያ ጨዋታ ከናሚቢያ ጋር 0ለ0 አቻ ተለያየና በምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ ባለፈው ማክሰኞ ከዚምባቡዌ ጋር ተጋጥሞ ግን 1ለ0 በመሸነፉ ግን ከውድድሩ ውጭ ሆኗል፡፡ በምድባቸው የመጨረሻ ጨዋታቸውን ከምትመጣጠናቸው ሞውሪሽዬስ ጋር ያደረጉት ለክብር ብቻ ነው፡፡ ዋና አሰልጣኙ ኡልሪች ማቲዮት ቡድናቸው በኮሳፋ ካፕ ሲሳተፍ በምድቡ በከፍተኛ የእግር ኳስ ደረጃ ላይ የሚገኙ ቡድኖችን ቢገጥምም ዋና ዓላማቸው በየትኛው ቡድን ላለመሸነፍ ነው ብለዋል፡፡ የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን በደቡብ አፍሪካ ላላፉት 2 ሳምንታት ተቀምጦ ጠንካራ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነበር፡፡ ማቲዩት በተጨማሪ አስተያየታቸው በቡድናቸው የኮሳፋ ካፕ ተሳትፎ አንዳንድ ተጨዋቾች በደቡብ አፍሪካ ክለቦች የሚገቡበትን እድል ከመፍጠሩም በላይ በቀጣይ በሚሳተፉባቸው አህጉራዊ የማጣርያ ውድድሮች የተሰጠውን ዝቅ ያለ ግምት ለማስተካከል ምቹ መድረክ ይፈጥርልናል ብለዋል፡፡ ሲሸልስ ከኮሳፋ ካፕ የምድብ ጨዋታዎች መሰናበቷ ብዙም የማያስቆጭ እንደነበር የገለፁት ዋና አሰልጣኙ ኡልሪች ማቲዮት፤ ባለፉት አመታት በሻምፒዮናው ሲሳተፉ በሁለት ጨዋታዎች እስከ ስምንት ጎሎች እንደተቆጠረባቸው አስታውሰው ዘንድሮ ግን አንድ ጎል ብቻ እንደተመዘገበበባቸው እና በመከላከል ረገድ ጥሩ ለውጥ ማየታቸው ተስፋ እንዳሳደረባቸው ተናግረዋል፡፡ የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን በነሐሴ ወር በህንድ ውቅያኖስ ዙርያ በሚገኙ ደሴቶች እና አገራት መካከል በሚደረግ ሻምፒዮናም ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡

አልጄርያ እስከ ኢትዮጵያ ግጥሚያ የወዳጅነት ጨዋታ  የላትም

የአልጄርያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት ፈረንሳዊው ክርስትያን ጉርኩፍ በምድባቸው ጠንካራ ተፎካካሪያቸው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን መሆኑን በተደጋጋሚ እየገለፁ ናቸው፡፡ ምድብ 10 ለአልጄርያ ቀላል ነው መባሉን በፍፁም አልቀበልም የሚሉት ጉርኩፍ፤ ለኢትዮጵያ ቡድን የተለየ ትኩረት ቢኖረንም ሌሶቶ እና ሲሸልስንም በቅርበት እንከታተላለን ይላሉ፡፡ ይህን አቋማቸውን በተግባር ለማሳየትም ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው የኮሳፋ ካፕን እየተመለከቱ ናቸው፡፡ በአልጄርያ ሊግ የሚገኙ ምርጥ ተጨዋቾችን በቡድናቸው ስብስብ ለማካተት ከፍተኛ ክትትል እያደረጉ ያሉት አሰልጣኙ ፕሮፌሽናሎቻቸውንም በሁሉም የምድብ ማጣርያዎች በተገቢው ጊዜ አሰባስበው ለመጠቀም እየሰሩ ናቸው፡፡

ለክርስትያን ጉርክፍ ዝግጅት ብቸኛዎቹ እንቅፋቶች በአውሮፓ ክለቦች የሚጫወቱ ተጨዋቾችን ለመሰብሰብ የሚፈጠሩ ውስብስብ ሁኔታዎች እና በተለይ በፊፋ የወዳጅነት ጨዋታዎች መርሃ ግብር መሰረት በመጀመርያዎቹ የምድብ ማጣርያ ሶስት ጨዋታዎች ለሚቀጥሉት ሶስት እና አራት ወራት ተጋጣሚ እንደሌላቸው መገንዘባቸው ነው ተብሏል፡፡ አንዳንድ የአልጄርያ ሚዲያዎች እንደገለፁት አረንጓዴዎቹ 2016 እኤአ እስኪገባ የወዳጅነት ጨዋታ የማያገኙ ሲሆን ምናልባት ግን በአዲሱ የፈረንጆች አመት ዋዜማ ከአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮና ኮትዲቯር ጋር የመያገናኛቸው የፊፋ የወዳጅነት ጨዋታ መርሃ ግብር የመጠቀም እድል እንዳላቸው አመልክተዋል፡፡

ኬንያ የቻን ማጣርያን በሜዳዋ ለመጨረስ ዝግጅቷ ቀጥሏል

በሩዋንዳ አዘጋጅነት በ2016 እኤአ ላይ ለሚደረገው 4ኛው የቻን ውድድር የሚደረገውን የመጀመርያ ጨዋታን ኬንያ በሜዳዋ በማስተናገዷ ደስተኛ እንደሆነች ዘገባዎች እያመለከቱ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያን ጠንካራ ተፎካካሪነት በሜዳቸው በሚያስመዘግቡት ውጤት በመጨረስ ለመልሱ ለመዘጋጀት እቅድ እንዳላቸው የገለፁት ዋና አሰልጣኙ ቦቢ ዊልያምሰን ለዝግጅታቸው ምንም አይነት እንቅፋት መኖር እንደሌለበት እያሳሰቡ ናቸው፡፡ የኬንያ ፕሪሚዬር ሊግ አስተዳዳሪዎች ለብሄራዊ ቡድን በሚለቀቁ ተጨዋቾች ዙርያ ሰሞኑን ያወጡት አዲስ ደንብ ይህን ማሳሰቢያቸውን ያከበረ አይደለም በሚል ተተችቷል፡፡ የፕሪሚዬር ሊጉ ክለቦች ተጨዋቾቻቸውን ለመልቀቅ ቅድመ መስፈርት ማቅረባቸው ከፌደሬሽኑ እና ከሃራምቤ ኮከቦች አሰልጣኝ ጋር ማጋጨት ጀምሯል። የአገሪቱ ክለቦች ለወዳጅነት ጨዋታ  ተጨዋቾቻቸውን የሚለቁት ግጥሚያው 2 ቀን ሲቀረው እንዲሆንና ለአህጉራዊ ውድድር ደግሞ ግጥሚያው 4 እና 5 ቀናት ሲቀረው ተስማምተዋል ተብሏል፡፡

የኬንያ ብሄራዊ ቡድን ስታርታይምስ በተባለ የቻይና ኩባንያ በ270 ሚሊዮን የኬንያ ሽልንግ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ስፖንሰር ተደርጓል፡፡

 

 

 

Read 2121 times