Saturday, 25 April 2015 11:12

የባሬቶ ምትክ ከየት እንደሚገኝ አልታወቀም

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ጋር የተፈራረመው የሁለት ዓመታት የኮንትራት ውል እንዲቋረጥ ተደረገ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከወር በኋላ በተለያዩ አህጉራዊ ውድድሮች የሚሳተፍ ሲሆን የዋና አሰልጣኙ ቅጥር ዝግጅቶችን በትኩረት ለማድረግ ወሳኝ ይሆናል፡፡ የዋና አሰልጣኙ ኮንትራት የፈረሰው ሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች በደረሱበት የጋራ ስምምነት መሠረት እንደሆነ ያመለከተው የፌዴሬሽኑ ህዝብ ግንኙነት፤ የአሰልጣኙ ስንብት በመከባበር ስሜትና በሠለጠነ አግባብ እንደተፈፀመ እንዲሁም ውሉን በማቋረጥ ሊከሰት የሚችለውን ውጣ ውረድ በማስወገድ ወደፊት በትብብር  ለመሥራት የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የሚያስች ነው ብሏል፡፡
የውል ስምምነቱ መቋረጡን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አንድ ዓመት በብሄራዊ ቡድኑ ለሰሩት አሠልጣኝ   ማሪያኖ ባሬቶ ተጨማሪ የሦስት ወር ደመወዝ ከፍሏቸዋል፡፡ ፌደሬሽኑ እና ማርያኖ ባሬቶ በተተኪ ወጣቶች ላይ የተጀመረው የእግር ኳስ ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ በመተባበር መንፈስና በጋራ ለመሥራት እንደተስማሙ ተገልፆ፤ አሠልጣኙ ወጣት ተጫዋቾች ከፍተኛ ሥልጠና እንዲያገኙ ለማድረግ የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው ለመቀጠል ቃል መግባታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሌላ በኩል ፖርቱጋላዊው ማርያኖ ባሬቶ በተለይ ለሱፕር ስፖርት በሰጡት አስተያየት በኢትዮጵያ ጥሩ እየሰሩ እንደነበር ተናግረው፤ ከቤተሰብ ጋር ለረጅም ጊዜ በሚያራርቀው ሃላፊነታቸው የተፈጠሩ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ለስንብታቸው  እንደ ዋና ምክንያታቸው ጠቅሰውታል፡፡  በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝነት ሲቀጠሩ ገና ከጅምሩ  በፌደሬሽኑ በኩል የተፈጠሩባቸው አንዳንድ ውስብስብ ችግሮች መኖራቸውን በማንሳትም በወቅቱ ከፌደሬሽኑ ይፈልጓቸው የነበሩ ድጋፎች በማነሳቸው ስራቸውን ወዲያውኑ ለመልቀቅ አመንትተው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በስንብታቸው ምንም ፀፀት እንደማይሰማቸው፤ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ወጣት ተጨዋቾችን በማሳደግ ባበረከቱት አስተዋፅኦ እንደሚደሰቱ ለሱፕር ስፖርት ያሳወቁት ማርያኖ ባሬቶ፤ ለቡድኑ መጭው ጊዜ የተሳካ እና በውጤት ያማረ እንዲሆንም ተመኝተዋል፡፡
የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ጁነዲን ባሻ በበኩላቸው ለሱፕር ስፖርት ሲናገሩ የአሰልጣኙ የቅጥር ኮንትራት የመጀመርያ ምዕራፍ ሊገባደድ የቀሩት 10 ቀናት እንደነበሩ ጠቅሰዋል፡፡ ከዋልያዎቹ በኋላ ለማርያኖ ባሬቶ  በስራ ዘመናቸው መልካሙን ሁሉ እንዲገጥማቸው የተመኙት ፕሬዝዳንቱ ምስጋናቸውን ለአሰልጣኙ አቅርበዋል።   የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት ስለ ብሄራዊ ቡድኑ ምትክ አሰልጣኝ ቅጥር ከሱፕር ስፖርት ለቀረበላቸው ጥያቄ ዝርዝር  ምላሽ ከመስጠት  ተቆጥበዋል፡፡
ማሪያኖ ባሬቶ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በፊት በብሄራዊ ቡድን ደረጃ ያሰለጠኑት ብቸኛው የጋና ብሄራዊ ቡድን ሲሆን የሰባት ወራት ቆይታ አድርገዋል፡፡ ከጋና እግርኳስ ማህበር ጋር የተስማሙትን የአሰልጣኝነት ውል ህገወጥ በሆነ መንገድ በማፍረስ ከሃላፊነት በመልቀቃቸው ፊፋ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ በገብቶ ውል በማፍረሳቸው  83 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ለጋና እግርኳስ ማህበር እንዲከፍሉ ቀጥቷቸው ነበር።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ፌዴሬሽኑ ማርያኖ ባሬቶን ካሰናበተ በኋላ ሃላፊነቱን የሚረከብ ባለሙያ ከየት እንደሚገኝ የታወቀ ነገር የለም፡፡ በተለያዩ ሁኔታዎች ለብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝነት ላለው  ክፍት የስራ ቦታ ላይ ሁነኛ ምትክ ለማግኘት አጠያያቁ ይሆናል። የመጀመርያው ባለሙያው የተፈለገው በብዙ አገራት የእግር ኳስ የውድድር ዘመኑ አጋማሽ ላይ ባለበት ወቅት መሆኑ ብቁ አሰልጣኝ የማግኘት እድሉን ስለሚያጠብበው ሲሆን፤ በሌላ በኩል በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ያው የአመራር ክፍተት እና ልዩነት የቅጥሩን ስኬታማነት እንደሚያስተጓጉል አስተያየት እየ

Read 2923 times