ያለ ሰዓቱ ከተበረከተ ወርቅ፣ በሰዓቱ የተወረወረ ድንጋይ ይሻላል፡፡
ችግር አንበሳን ቀበሮ ያደርጋል፡፡
የተፈታ እንቆቅልሽ ቀላል ይመስላል፡፡
ሁሉም ሰው የእንጀራው ንጉስ ነው፡፡
ብልህ ሰው በራሱ ቀልድ መሳቅ ይችላል፡፡
የበዛ ሙገሳ ከስድብ ይቆጠራል፡፡
ገነት ያለው ከእናት እግር ሥር ነው፡፡
ከባዕድ ጋር ኤደን ውስጥ ከመቀመጥ ከወዳጆቹ ጋር ወህኒ ቤት መታሰር ይሻላል፡፡
ጓደኛና ግጥም አንድ ናቸው፡፡
ህፃናት የገነት ድልድይ ናቸው፡፡
ከጅል ጓደኛ ብልህ ጠላት ይሻላል፡፡
ደምን በደም ማጠብ አይቻልም፡፡
ጠብታ ሲጠራቀም ባህር ይሆናል፡፡
እስከ ንጋት ድረስ የሚበራ ላምባ የለም፡፡
ዓይነ ስውር በመላጣ ይስቃል፡፡
ልብ ለሌላቸው ልብህን አትስጥ፡፡
ድመት ልጆቿን መብላት ሲያምራት አይጦች ይመስላሉ ትላለች፡፡
ጥሩ ዓመት በፀደይ ያስታውቃል፡፡
ሁለት አዋላጆች የህፃን አንገት ይቀጫሉ፡፡
Published in
ህብረተሰብ