Monday, 16 March 2015 10:09

ልጅ ያሬድ በዋሽንግተን ሆቴል ኮሜዲ ማቅረብ ጀመረ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(6 votes)

ለየት ባለ የኮሜዲ አቀራረቡ እውቅናን የተቀዳጀው ልጅ ያሬድ፤በየሳምንቱ ረቡዕ ከ12፡00 እስከ3፡00 ሰዓት የሚዘልቅ ስታንዳፕ ኮሜዲ በዋሽንግተን ሆቴል ማቅረብ የጀመረ ሲሆን የመጀመሪያ ዝግጅቱን ባለፈው ረቡዕ ምሽት አቅርቧል፡፡ ኮሜዲያኑ በአሜሪካ ቆይታው በተለያዩ ስቴቶችና መድረኮች ላይ ያቀረባቸው ስራዎችም በዶክሜንታሪ መልክ በአጭሩ ታይተዋል፡፡
ልጅ ያሬድ ከኮሜዲ ስራው ባሻገር የስዕል ስራዎቹንና በወዳደቁ ቁሳቁሶች የተጠበበባቸውን አስገራሚ ቅርፃ ቅርፆች በመድረክ ላይ አቅርቦ ታዳሚውን አስደንቋል፡፡ ያለፈው ረቡዕ የመክፈቻ ፕሮግራም በ“ንጉስ ፕሮሞሽን ኤንድ ኤቨንትስ” አስተባባሪነትና በቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ስፖንሰርነት የቀረበ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ ዝግጅቱን ስፖንሰር በማድረግ ይዘልቃል ተብሏል፡፡

Read 4249 times