Monday, 09 March 2015 12:14

“ወንድ አይገባም” ቴአትር ሰኞ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

በአንጋፋዋ የኪነ - ጥበብ ባለሙያ አለምጸሀይ በቀለ ተደርሶና ተዘጋጅቶ በጄአይዲ የኪነጥበብ ፕሮሞሽንና ቴአትር ኢንተርፕራይዝ  የሚቀርበው “ወንድ አይገባም” የተሰኘ ሳታየር ኮሜዲ ቴአትር የፊታችን ሰኞ በሐገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከ11፡00 ሰዓት ጀምሮ ይመረቃል፡፡
እያዝናና ያስተምራል በተባለው በዚህ ቴአትር ላይ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን የሚሳተፉ ሲሆን ጀምበር አሰፋ፣ ቅድስት ገ/ስላሴ፣ መሰረት መኮንን፣ መክሊት ገብረየስ፣ ማርታ ጌታቸው፣ ባንቺአምላክ ስለሺና ሌሎችም ይተውኑበታል፡፡ ቴአትሩ ከነገ ወዲያ በሐገር ፍቅር ከተመረቀ በኋላ ዘወትር ሰኞ በዚሁ ቴአትር ቤት ለተመልካች መቅረብ ይጀምራል፡፡  

Read 915 times