Monday, 09 March 2015 11:53

“በሳል አምደኞች ይጨመሩበት”

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ዳንኤል ክብረት
(ፀሐፊና ተመራማሪ)
      “በአገራችን የግል ፕሬስ ታሪክ ለረጅም ጊዜ ሳይቋረጡ ከቆዩ ጋዜጦች መካከል አንዷ አዲስ አድማስ ነች፡፡ ብዙዎቹ በተለያዩ ምክንያቶች እጣ ፈንታቸው መቋረጥ ሆኖ ተለይተውናል፡፡  በሁሉም እድሜ ክልል ውስጥ ያሉ አንባቢያን ሊያነቡት የሚችሉት ጋዜጣ ናት ብዬ አስባለሁ፡፡
ጋዜጣዋ በማህበራዊና በመዝናኛ ጉዳዮች ላይ የምታተኩር ሲሆን ዜናዎቿም በሰዎች ጉዳይ ላይ ትኩረት  ተደርጎ የሚሰራና “የእኔ” የሚል ስሜትን የሚፈጥር ነው፡፡ በጋዜጣው ላይ ቢስተካከሉ የምላቸው ጉዳዮች ቢኖሩ፣ አምዶች በጉልህ ሊለዩ የሚችሉበት ነገር ቢፈጠር፤ አንድ ሰው ማንበብ የሚፈልገውን አምድ የለመደበት ቦታ ላይ ሄዶ ማንበብ የሚችልበት መንገድ ቢመቻች ጥሩ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ጠንከር ጠንከር ያሉ ፅሁፎች ሊያቀርቡ የሚችሉ አምደኞች ቢጨመሩበት የበለጠ ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡
እንግዲህ በቀጣይ የሥራ ዘመናችሁ ጋዜጣዋ የበለጠ እያደገች፣ እየታረመች፤ በኢትዮጵያ የፕሬስ ታሪክ ውስጥ ዘልቃ የምትቀጥል ሆና አባቶቻችን፣ እኛም፣ ልጆቻችንም፣ የልጅ ልጆቻችንም የሚያነቧት ሆና እንድትቀጥል ምኞቴ ነው፡፡

Read 3247 times