“የጥቁሮች ታሪክ ወር” ተብሎ የሚጠራውን የየካቲትን ወር ምክንያት በማድረግ በአሜሪካ ኤምባሲ ድጋፍ የተዘጋጀና በአፍሪካ አሜሪካዊ ሴት ሰዓሊያን ስራዎች ላይ ያተኮረ “የአፍሪካ አሜሪካዊ ሴቶች የስዕል ስራ ከ19-21ኛው ክፍለ ዘመን” የተሰኘ የስዕል ትርኢት ሰሞኑን በብሄራዊ ሙዚየም የተከፈተ ሲሆን በክልል ከተሞችም ይቀርባል ተብሏል፡፡ ስዕሎቹ በ1943 እ.ኤ.አ ጄምስ ቪ ሄሪንግ እና አሎንዞ ጄ ኤደን በተባሉ ሁለት አፍሪካ አሜሪካዊ ፕሮፌሰሮች በተመሰረተው “ባረንት ኤደን ኮሌክሽን” ጋለሪ ውስጥ ተቀምጠው እንደነበር የተገለፀ ሲሆን በትውልድ ጃማይካዊት በዜግነት አሜሪካዊት በሆነችው ዶ/ር ደስታ ሚግ አስተባባሪነት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ለእይታ እንደበቁና አሜሪካ ኤምባሲም ዝግጅቱን ስፖንሰር እንዳደረገ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ባለፈው ረቡዕ ተከፍቶ በዚያኑ እለት ምሽት በተዘጋው የስዕል ትርዒት ላይ የቀረቡት 40 ስዕሎች ከሶስት መቶ ዓመታት በፊት አፍሪካ አሜሪካዊያን ስላሳለፉት የባርነት ዘመን፣ የነፃነት ትግል፣ እንዲሁም ስለ ባህላቸው፣አለባበሳቸውና ማንነታቸው የሚገልጹ ናቸው ተብሏል፡፡ ስዕሎች ከመጋቢት እስከ ሚያዝያ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ በባህር ዳር፣ በድሬደዋ፣ በሃረር እና በጅማ ለእይታ ይበቃሉ ተብሏል፡፡
Monday, 02 March 2015 10:27
የአፍሪካ አሜሪካዊ ሴቶች የስዕል ስራ በክልሎች ይቀርባል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና