Saturday, 21 February 2015 13:45

“ፀሃዬ ደመቀች” የመዝሙር ሲዲ ለገበያ ቀረበ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(6 votes)

አባታቸውን በውትድርና ያጡና ጎዳና ላይ ተጥለው የተገኙ ህፃናትን ለማሳደጊያነት ታስቦ በ1973 ዓ.ም የተመሰረተው የ“ዝዋይ ህፃናት አምባ” ልጆች እየዘመሩ ካደጉባቸው መዝሙሮች መካከል 12ቱን  ያካተተ “ፀሀዬ ደመቀች” የተሰኘ የመዝሙር ሲዲ ለገበያ ቀረበ፡፡
ሲዲው በተለይ በአገርና በወላጅ ፍቅር እንዲሁም  በአፍሪካ ጉዳይ ላይ የሚያተኩሩ መዝሙሮችን እንደያዘ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እየዘመሩ ያደጉባቸውን መዝሙሮች እንደገና በሲዲ ለማሳተም የተፈለገው በዕድሜ ከፍ ላሉ ልጆች መዝሙር ባለመኖሩና የህጻናት አምባ ቆይታቸውን ለማስታወስ እንደሆነ ታውቋል፡፡
ሲዲው በህጻናት አምባው ውስጥ ባደገው ዘውዱ ዳምጠው መቀናበሩንና ወደፊት ሁሉም መዝሙሮች ቪዲዮ ክሊፕ እንደሚሰራላቸው የተጠቆመ ሲሆን “ፀሀዬ ደመቀች” በ25 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ በዝዋይ ህጻናት አምባ ውስጥ 7ሺህ ያህል አባት የሌላቸው ህጻናት እንዳደጉ  ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 3306 times