የቱሪዝም ጋዜጠኛው ሄኖክ ስዩም ያዘጋጀው “የመንገድ በረከት” የተሰኘ መፅሀፍ በመጪው አርብ ከቀኑ 10፡30 ሰዓት ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ-መፃህፍትና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡
መፅሀፉ በአገራችን አራቱም አቅጣጫዎች ጋዜጠኛው ተዘዋውሮ የጎበኛቸውን የቱሪስት መስህቦች የሚያስቃኝ ሲሆን ከአንድ ወር በፊት ለንባብ መብቃቱ ይታወሳል፡፡ ሄኖክ ስዩም የሃገሬ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መስራችና ስራ አስኪያጅ ሲሆን በየወሩ ቱሪዝም ላይ አተኩሮ የሚወጣው “ቱባ” መፅሄት አሳታሚም ነው፡፡
Saturday, 21 February 2015 13:43
“የመንገድ በረከት” መፅሀፍ ይመረቃል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና