Saturday, 21 February 2015 13:43

“የመንገድ በረከት” መፅሀፍ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

የቱሪዝም ጋዜጠኛው ሄኖክ ስዩም ያዘጋጀው “የመንገድ በረከት” የተሰኘ መፅሀፍ በመጪው አርብ ከቀኑ 10፡30 ሰዓት ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ-መፃህፍትና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡
መፅሀፉ በአገራችን አራቱም አቅጣጫዎች ጋዜጠኛው ተዘዋውሮ የጎበኛቸውን የቱሪስት መስህቦች የሚያስቃኝ ሲሆን ከአንድ ወር በፊት ለንባብ መብቃቱ ይታወሳል፡፡ ሄኖክ ስዩም የሃገሬ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መስራችና ስራ አስኪያጅ ሲሆን በየወሩ ቱሪዝም ላይ አተኩሮ የሚወጣው “ቱባ” መፅሄት አሳታሚም ነው፡፡

Read 1106 times