በ17 ዘርፎች ተከፍሎ ለወራት ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው ዙር የጉማ ፊልም ሽልማት ውድድር አሸናፊዎች ከነገ ወዲያ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴአትር ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በሚደረገው ሥነስርዓት እንደሚሸለሙ የፕሮግራሙ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡ በኢትዮ ፊልምስ ባለቤትነት በተዘጋጀው በዚህ ውድድር፤ ከ17 ዘርፎች ምርጥ አምስቶቹ ባለፈው ጥር 7 ቀን 2007 ዓ.ም በሃርመኒ ሆቴል ይፋ የተደረጉ ሲሆን የፊታችን ሰኞ የመጨረሻዎቹ አሸናፊዎች ለክብር ሽልማት ይበቃሉ ተብሏል፡፡ በሥነ ሥርዓቱ ላይ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ፊልም አፍቃሪዎች፣ አምባሳደሮች፣ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ በእለቱ በበደሌ ቢራ የገንዘብ ሽልማት የሚደረግለት አንድ ባለሙያ እንዳለ የጠቆሙት አዘጋጆቹ፤ተሸላሚው ማን እንደሆነ እንደማያውቁና ሽልማቱም ሰርፕራይዝ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የሽልማት ስነ-ስርዓቱ በቀይ ምንጣፍ ሥነ ሥርዓት እንደሚካሄድ ተጠቁሟል፡፡
Saturday, 21 February 2015 13:36
የጉማ ፊልም ሽልማት ሥነስርዓት ሰኞ ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና