Saturday, 21 February 2015 13:03

ወንጀል-ነክ እንቆቅልሾች?

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ሰውየው የሆቴል ክፍል ውስጥ ጋደም ብሎ በር ይቆረቆራል፡፡ ከአልጋው ውስጥ ይወጣና በሩን ይከፍታል፡፡ በሩ ላይ የቆመው የማያውቀው እንግዳ ሰው ነበር፡፡ እንግዳውም እየተጣደፈ፤ “ይቅርታ አድርግልኝ፤ ሳልሳሳት አልቀረሁም፤ የእኔ ክፍል መስሎኝ ነው” ይልና ከመቅፅበት የፎቁን ደረጃ ወርዶ ይሄዳል። ሰውየው የክፍሉን በር ዘግቶ ሲያበቃ የሆቴሉ የፀጥታ ሰራተኞች ጋ ይደውልና በሩን የቆረቆረውን ሰውዬ በፍጥነት እንዲይዙት ይጠቁማቸዋል፡፡
ለምንድነው በሩን የቆረቆረው ሰውዬው
እንዲያዝ የጠቆመው?
ሰውየውን ለመጠርጠርስ ምንድነው
ያበቃው?
አንድ ሽማግሌ በተንጣለለ ሰፊ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ለብቻቸው ይኖራሉ። በዕድሜያቸው መግፋት የተነሳ እንደልባቸው መንቀሳቀስ ስለማይችሉ የሚያስፈልጓቸው ነገሮች ሁሉ እቤታቸው ድረስ ይመጡላቸዋል።
አርብ ዕለት ፖስተኛው ፖስታ ሊያደርስ
ሲመጣ አካባቢው ጭር ይልበትና አንድ
ነገር ጠርጥሮ፣ በበሩ ቁልፍ ቀዳዳ አጮልቆ
ይመለከታል፡፡ ባየው ነገርም ይደነግጣል
ሽማግሌው ወለሉ ላይ በደም ተለውሰው
ይታያሉ፡፡
የወንጀል መርማሪ ከመቅጽበት ከስፍራው
ይደርሳል፡፡
መርማሪው፤ ከመኖሪያ ቤቱ ውጭ ሁለት
ጠርሙስ ወተት፣ የማክሰኞ ጋዜጣ፣ ጥቂት
ያልተከፈቱ ፖስታዎችና ስጦታዎችን
ያገኛል። መርማሪው ነፍሰ ገዳዩን ለማወቅ
ጊዜ አላጠፋም፡፡
ነፍሰ ገዳዩ ማነው?

መልስ
በሩን የቆረቆረው እንግዳ ሰውዬ “የእኔ ክፍል መስሎኝ ነው” ብሎ ነበር፡፡ እንዲያ ቢሆን ኖሮ ግን የክፍሉን ቁልፍ መያዝ ነበረበት፤ በሩንም መቆርቆር አልነበረበትም፡፡
ነፍሰ ገዳዩ፤ ጋዜጣ አዳዩ ሰውዬ ነው፤ ምክንያቱም የረቡዕና ሐሙስ ጋዜጦችን አላመጣም፡፡  ይሄንንም ያደረገው ጋዜጦቹን የሚያነብ እንደሌለ ስላወቀ ነው፡፡


Read 3840 times