Saturday, 24 January 2015 13:52

“የገጠር ልጅ” ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በእውነት ፊልም ፕሮዳክሽን የተሰራውና በወንድወሰን ይሁብ ተደርሶ በእውነት አሳሳህኝና በደራሲው የተዘጋጀው “የገጠር ልጅ” የተሰኘው ፊልም ነገ ከቀኑ 11፡30 በብሔራዊ ቲያትር በሚካሄድ ሥነ ስርአት ይመረቃል፡፡ ቤተሰቦቿን ለመርዳት ወደ አረብ አገር በስደት ሄዳ ወደ ሀገሯ የተመለሰች አንዲት ወጣት የሚደርስባትንና የሚያጋጥማትን አሳዛኝ የህይወት ፈተና የሚያሳየው ልብ አንጠልጣይ ፊልም ሙሉ ቀረፃው የተካሄደው በአዲስ አበባ ከተማና ሰንዳፋ አካባቢ መሆኑን የፊልሙ ፕሮዲዩሰሮች ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ በፊልሙ ላይ ተሻለ ወርቁንና ሰለሞን ሙሔን ጨምሮ ከ90 በላይ ወጣትና አንጋፋ ተዋንያን የተሳተፉበት መሆኑ ተገልጿል፡፡

Read 1698 times