ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ሰንዳፋ ከተማ “ዋን ስቶፕ ሲኒማ” የተሰኘ ዘመናዊ ሲኒማ ቤት ባለፈው ሳምንት ተመርቆ አገልግሎት ጀመረ፡፡ ሲኒማ ቤቱ በ1.7 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ ሲሆን ለከተማዋና ለአካባቢው ነዋሪዎች አማራጭ የመዝናኛ ማዕከል ይሆናልም ተብሏል፡፡ ሲኒማ ቤቱ እስከ 500 የሚደርሱ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም እንዳለው ተገልጿል፡፡ በከተማው ከንቲባ አቶ ዘገዬ ካሳ የዛሬ ሳምንት ተመርቆ የተከፈተው ዋን ስቶፕ ሲኒማ፤ ለአገሪቱ የፊልም ኢንዱስትሪ እድገት የበኩሉን ድርሻ እንደሚያበረክት የድርጅቱ ባለቤት አቶ ዘላለም ተመስገን ተናግረዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና