13ኛው የጋለሪያ ቶሞካ ፖርትሬይት አርት የስዕል ኤግዚቢሽን በሚቀጥለው አርብ “ስዕላዊ ቀልድ እና ስዕላዊ ምፀት” በሚል ርዕስ ይከፈታል፡፡ የሰዎችን ምስል በማጋነን አስቂኝና አዝናኝ በማድረግ በሚታወቀው ቴዎድሮስ መስፍን (ቴዲ ማን) የተሰሩ 30 ያህል የሰው ምስሎች በአዝናኝ መልክ የሚቀርቡ ሲሆን ታዋቂ የውጭና የአገር ውስጥ ሰዎች ምስል ተካቶበታልም ተብሏል፡፡ በመጪው አርብ ረፋድ ላይ የሚከፈተው ይህ ፖርትሬት አርት ኤግዚቢሽን፤ ሳር ቤት ካናዳ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው ቶሞካ አርት ጋለሪ ውስጥ ለቀጣዮቹ ሁለት ወራት ለእይታ ክፍት ሆኖ ይቆያል ተብሏል፡፡
Saturday, 24 January 2015 13:35
“ስዕላዊ ቀልድና ስዕላዊ ምፀት” የስዕል ኤግዚቢሽን ይከፈታል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና