በተለያዩ የኪነጥበብ ስራዎች ላይ የተሰማራው የዶን ፊልሞች ፕሮዳክሽን የገጣሚ በአካል ንጉሴ የግጥም ስብስቦችን ያካተተውን “ፍላሎት” የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ባሳለፍነው ሳምንት አጋማሽ በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ አዳራሽ አስመርቋል፡፡
መጽሐፉ በማህበራዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ 68 ግጥሞችን ያካተተ ሲሆን በ91 ገፆች ተቀንብቦ በ25 ብር ለገበያ እንደቀረበ ታውቋል፡፡ በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ ተፈሪ አለሙ፣ ኪሮስ ሃ/ስላሴ፣ ምስራቅ ተረፈና እምወድሽ በቀለ ከመጽሐፉ ላይ ግጥሞችን ለታዳሚው አቅርበዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና