በገጣሚ እርቅይሁን በላይነህ የተፃፈው “እርቃንሽን ቅሪ” የተሰኘ የግጥም መድበል ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቴአትር ጥበባት መምህር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ጀዋሬ በመፅሃፉ ጀርባ ላይ ባሰፈሩት አስተያየት፤ በመድበሉ የተካተቱት ግጥሞች ጠንካራ እንደሆኑ ጠቁመዋል፡፡
በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የቴአትር ጥበባት መምህር የሆኑት ጋዜጠኛ አስተዋይ መለስ በበኩላቸው፤ “ታሪክን የሚያወሱ ጥሩ ግጥሞች ናቸው” ሲሉ አድንቀዋል፡፡ በ132 ገፆች 77 ግጥሞችን ያካተተው መፅሀፉ፤ በ25 ብር ለሽያጭ ቀርቧል፡፡
ገጣሚው ከዚህ ቀደም “ያልተጠቡ ጡቶችን” የተሰኘ የአጫጭር ልብወለድ መድበልና “የኢትዮጵያ ታሪክ ከኢማም አህመድ እስከ አጼ ቴዎድሮስ” የሚል የታሪክ መፅሃፍ ለንባብ ማብቃታቸው ይታወሳል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና