Saturday, 30 August 2014 11:22

“ድፍረት” ፊልም ሃሙስ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

በዘረሰናይ መሃሪ ተፅፎ የተዘጋጀውና በእውቋ የፊልም ኮከብ ተዋናይ አንጀሊና ጆሊ ፕሮዲዩስ የተደረገው “ድፍረት” ፊልም የፊታችን ሐሙስ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡ በአሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በተመልካች ምርጫ አሸንፎ ለሽልማት የበቃውና በአንዲት ኢትዮጵያዊት የገጠር ታዳጊ እውነተኛ የጠለፋ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው ፊልሙ፤ በ64ኛው የበርሊን ዓለም አቀፍ ፊልም ፌስቲቫል ላይ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ ዓለም አቀፍ አድናቆት የተቸረው ይሄ ፊልም በሚቀጥለው ሃሙስ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የፊልሙ ደራሲና ዳይሬክተር ዘረሰናይ መሃሪና በፊልሙ ላይ የተሳተፉት ተዋንያንና እንዲሁም ታሪኳ በፊልሙ የተካተተው የህግ ባለሙያዋ መዓዛ አሸናፊ በተገኘችበት እንደሚመረቅ የፕሮግራሙ አዘጋጅ “ሃይሌ ፒክቸርስ” ለአዲስ አድማስ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡

Read 2109 times