Saturday, 09 August 2014 11:47

“የብርሃን ፊርማ” የተሰኘ ፊልም ሰኞ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

በእስክንድር ዋሴ ተደርሶ፣ በሄኖክ ለማ እና በኢያሱ እንዳለ የተዘጋጀው “የብርሃን ፊርማ” የተሰኘ ፊልም የፊታችን ሰኞ ከቀኑ በ11፡00 ሰዓት በብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል፡፡ በ“ሱዛና ፒክቸርስ ፊልም ፕሮዳክሽን” የቀረበውና የድራማ ዘውግ ያለው ፊልሙ፣ በዋና ፕሮዲዩሰር እስክንድር ዋሴና በፕሮዲዩሰር ጋዜጠኛ ፅዮን ግርማ እንደተሰራ ታውቋል፡፡ የ1፡30 ርዝመት ያለው ፊልሙ፤ አንዲት በሙዚቃ ፍቅር የተማረከች እናት የህይወትን ውጣ ውረድና መሰናክል ለማለፍ ስትታትር የሚያሳይ ሲሆን ስኬትን፣ እናትነትንና ወጣትነትን የሚያስቃኝ ነው ተብሏል፡፡ በፊልሙ ላይ ሳያት ደምሴ፣ ታደለ ሮባ፣ ማህሌት ሹመቴ፣ ህፃን ማራኪ ዜና፣ ኤልያስ ወሰንየለህና አንዱአለም ተስፋው እንደተሳተፉበት “ሱዛና ፒክቸርስ ፊልም ፕሮዳክሽን” በላከው መግለጫ ጠቁሟል፡፡  

Read 1712 times