የጐንደር ዩኒቨርስቲን የ60 አመት ጉዞ የሚዘክር “የስልሳ ገፆች ወግ” የተሰኘ መጽሐፍ ታትሞ ለንባብ በቃ፡፡ በጋዜጠኛ አብርሃም ዘሪሁን የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ በሁለት ምዕራፎች የተቀናበረ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ ስለ ጐንደር ዩኒቨርስቲ አመሠራረትና ዛሬ የደረሰበትን ደረጃ ሲተነትን ሁለተኛው ምዕራፍ ለዩኒቨርስቲው እድገት አስተዋጽኦ ያበረከቱ ምሁራንን ይዘክራል፡፡
የመጽሐፉ ዋጋ 100 ብር ሲሆን ገቢው ለዩኒቨርስቲው ይውላል ተብሏል፡፡
በሌላ በኩል፤ በአሸናፊ ውዱ የተፃፈው “ሚስት መሆን” የተሰኘ የወግ መጽሐፍ ከትናንት በስቲያ ሀሙስ ምሽት ሰዓት በራስ ሆቴል ተመርቋል፡፡ በ196 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ በአንድ ሚስቱን በሞት ያጣ ባልና ከሴት ልጁ ጋር አጉል ድርጊት ውስጥ በገባ አባት ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን በ50 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና