Monday, 14 April 2014 08:52

ኢትዮጵያ ከሰብ ሳህራ አፍሪካ አገራት በወታደራዊ ሃይል ቀዳሚ ናት ተባለ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

ከግብጽና ከአልጀሪያ ቀጥላ በአፍሪካ 3ኛ ናት

ኢትዮጵያ ከሰሃራ በታች ከሚገኙ የአፍሪካ  አገራት ጠንካራ ወታደራዊ ሃይል በመገንባት የመጀመሪያውን ስፍራ እንደምትይዝ በ“ግሎባል ፋየር ፓወር” የተሰራ ጥናት አመለከተ፡፡
 “ግሎባል ፋየር ፓወር” 40 ያህል የተለያዩ መስፈርቶችን በመጠቀም የአገራትን ወታደራዊ አቅም ለመፈተሽ  የሰራው አዲስ ጥናት እንደሚያሳየው፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 182 ሺህ ያህል በስራ ላይ የሚገኙ ወታደሮች ያሏት ሲሆን  ከ24 ሚሊዮን የሚበልጡ ዜጎቿም በውትድርና መስክ ለመሰማራት አቅም ያላቸው ናቸው፡፡
ከ560 በላይ ታንኮችና ከ780 በላይ የወታደራዊ ተሸከርካሪዎች ያሏት ኢትዮጵያ፣ በአህጉሩ ጠንካራ ከሚባሉ አየር ሃይሎች የአንዱ ባለቤት መሆኗን የሚጠቅሰው ጥናቱ፣ አየር ሃይሉ ከ81 በላይ የጦር አውሮፕላኖችና 8 ተዋጊ ሂሊኮፕተሮች እንዳሉትም ገልጿል፡፡
አገሪቱ ለመከላከያ የምትመድበው አመታዊ በጀት 340 ሚሊዮን  ዶላር መድረሱን የጠቆመው ጥናቱ፣ ኢትዮጵያ ከግብጽና ከአልጀሪያ ቀጥላ በአፍሪካ አህጉር ጠንካራ የመከላከያ ሃይል ያላት ሶስተኛዋ አገር ናት ብሏል፡፡

Read 1902 times