በመጀመሪያ በእንግሊዝኛ ተሰርቶ፣ በአማርኛ ተተርጉሞ የተተረከው “የጥፋት ውሀ” የተሰኘ መንፈሳዊ ፊልም ነገ ከ8 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሄራዊ የባህል ማእከል ይመረቃል፡፡ በእንግሊዝኛው “The Creation and the Flood” የተሰኘውን ይህን ፊልም ወደ አማርኛ በመተርጎም፣ በማዘጋጀት እና በዋና ተራኪነት የሰራው አርቲስት ፈለቀ የማር ውሃ አበበ ሲሆን የአርቲስቱ ልጅ ህፃን በረከት ፈለቀ አበበና ባለቤቱ አበባ ወልዴ በትረካ ተሳትፈዋል፡፡ ፊልሙ ከዘፈጥረት ጀምሮ በኖህ ዘመን እስከተከሰተው የጥፋት ውሀ ድረሱ የነበሩ ሂደቶችን የሚያስቃኝ ነው ተብሏል፡፡