Saturday, 30 November 2013 10:39

ሶስት ሱሪዎችን ደራርቦ በመልበስ ሠርቆ ሲወጣ የተያዘው ተፈረደበት

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(4 votes)

የእህል ወፍጮ ሚዛን  የሰረቀው የ4 ዓመት እስር ተበይኖበታል

ከሌሊቱ 9 ሠአት ላይ በካዛንቺስ፣ መኖሪያ ቤት ግቢ ውስጥ ታጥበው የተሰጡ 3 ጅንስ ሱሪዎችን ደራርቦ በመልበስ

ሠርቆ ሲወጣ የተያዘው  ተከሣሽ ሀቢብ አብደላ ኑሪ፤ በፈፀመው ወንጀል በ2 አመት እስራት እንዲቀጣ የፌደራሉ ከፍተኛ

ፍ/ቤት  ሠሞኑን ብያኔ ሰጥቷል፡፡
ተከሣሹ የዛሬ ሦስት ሳምንት ህዳር 2 ሌሊት በልደታ ክፍለ ከተማ፣ ጥይት ፋብሪካ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ

መኖሪያ ግቢ እያንዳንዳቸው 600 ብር የሚያወጡ ሶስት ጅንስ ሱሪዎችን የራሱ አስመስሎ ደራርቦ በመልበስ ሰርቆ

ሲወጣ መያዙ  ተገልጿል፡፡ ፍ/ቤቱም ሠሞኑን “የተከሣሹ ድርጊት ሌሎችንም ያስተምራል” በሚል በ2 አመት እስራት

እንዲቀጣ ወስኗል፡፡
በሌላ በኩል በልደታ ክ/ከተማ የግለሠቦችን መኖሪያ ግቢ ሠብሮ በመግባት 5ሺህ ብር የሚገመት የእህል ወፍጮ ሚዛን

የሠረቀውና በሊስትሮነት የሚተዳደረው ወጣት ሠለሞን ፀጋዬ ላይ የ4 አመት እስራት በይኖበታል፡፡

Read 2185 times