Monday, 18 November 2013 11:55

“ኦቴሎ” በትግርኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ለንባብ ቀረበ

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(1 Vote)

             የእንግሊዛዊው ፀሐፌ ተውኔት ዊሊያም ሼክስፒር ድንቅ የተውኔት ስራ የሆነው “ኦቴሎ” በትግርኛ ቋንቋ ተተርጉሞ በመፅሃፍ ወጣ፡፡ ተውኔቱን ወደ ትግርኛ ለመመለስ አንድ ዓመት እንደፈጀበት ያስታወሰው አንጋፋው ደራሲና መምህር ኃይለመለኮት መዋዕል፤ ለዚህ ሥራው ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የተረጎመውንና በርካታ የተውኔቱን የእንግሊዝኛ ቅጂዎች እንደተጠቀመ ገልጿል፡፡ ተውኔቱ ለመድረክ ይበቃ እንደሆነ የተጠየቀው ተርጓሚው፤ መፅሃፉን ያሳተመው በብድር እንደሆነና ለመድረክ ዝግጅት አቅም እንደሌለው ጠቅሶ፤ ስራውን ያዩ ግለሰቦች ግን ወደ መድረክ ሊለውጡት እንደሆነ ተናግሯል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፎክሎር ዶክትሬት ዲግሪ ተማሪ ገዛኸኝ ፀጋውና ሌሎች ተባባሪዎች ባደረጉት ጥረትም የትግርኛ ቋንቋ በሚሰጥባቸው ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆች መፅሃፉ ለማስተማርያነት ሊሰራጭ እንደሆነ አክሎ ገልጿል፡፡
120 ገፆች ያሉት “ኦቴሎ” የተውኔት መፅሃፍ፤ በአይናለም፣ በሜጋ እና በዩንቨርሳል መፃህፍት መደብሮች በ30 ብር ለሽያጭ ቀርቧል፡፡ ኃይለመለኮት ተውኔቱን በ1964 ዓ.ም የተረጎመው ሲሆን በአብዮቱ ጊዜ መሰል መፅሃፍት ተሰብስበው ሲቃጠሉ በወንድሙ አማካኝነት ቆፍሮ በመቅበር፣ ከ42 ዓመታት በኋላ አሻሽሎ ለንባብ እንዳበቃው ገልጿል፡፡

Read 1965 times