የኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድን 1500ኛ ዓመት ልደት የተመለከተ አውደጥናት ዛሬ እንደሚካሄድ በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ማህበረ ቅዱሳን አስታወቀ፡፡ ዛሬ ከጧቱ 2፡30 እስከ 11፡30 በግዮን ሆቴል በሚደረገው የአንድ ቀን አውደጥናት የቅዱስ ያሬድ ልደትና የምናኔ ሕይወት፣ ዜማና ድርሰት፣ የቅዱስ ያሬድ ድርሳናት ከነገረ መለኮት አንፃር፣ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ተፅእኖ በባህላዊና ዘመናዊ ሙዚቃ የሚሉ ርእሶች ለውይይት ይቀርባሉ፡፡ ከዚህ በተያያዘም ነገ ከቀኑ 7 እስከ 11 ሰዓት የቅዱስ ያሬድ ልደትን የተመለከተ ሲምፖዚየም በኢትዮጵያ የስብሰባ ማእከል መዘጋጀቱን ማህበሩ አስታውቋል፡፡