Saturday, 09 December 2023 00:00

በመዲናዋ በሚገኙ 298 ት/ ቤቶች የስፖርት ስልጠናዎች ሊጀመር ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ ከኤሴቅ ዲኮርና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ጋር ባለፈው አርብ አራት ኪሎ በሚገኘው ወወክማ አዳራሽ ፣ባዘጋጀው የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የስፖርት ፌደሬሽኖች በተገኙበት፣ የጋራ ውይይትና ምክክር ተካሄደ፡፡ በዚህ ዝግጅት በ298 ት/ ቤቶች በ149
የት/ ቤት አዳራሾች የስፖርት ስልጠናዎች እንደሚጀመር የተገለጸ ሲሆን፤ ይህንንም ስራ ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ አሰልጣኞችን በመመደብ፣ ስልጠናው በመስጠት፣ ውድድሮችን በማዘጋጀት እንዲሁም ኤሴቅ ዲኮር እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር በትምህርት ቤት ያሉ አዳራሾችን ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ በማዘጋጀት በጋራ እንደሚያከናውኑት ተጠቁሟል፡፡


የውይይቱና ምክክሩ ዋነኛ አላማ ፣ ሁሉም የቴኳንዶ፣ የማርሻል አርት ባለሙያዎች በጋራ ሆነው እየተመካከሩ በመስራት ይህን የስፖርት ዘርፍ ለማጠናከርና ከፍተኛ ተሰጥቶት ማህበረሰቡ ዘንድ ተወዳጅ እንዲሆን ማስቻል ነው። ኤሴቅ ዲኮር እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር “ ትምህርት ለትውልድ“ በሚል መርህ፣ ከሃምሌ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወጣቶችን ከተለያዩ ሱሶችና ከአልባሌ ቦታ ለመጠበቅ አቅዶ በመነሳት፣ ከት/ሚር ስምምነት በመፈጸም ወደ ስራ የገባ መንግስታዊ ያልሆነ የግል ድርጅት ነው ተብሏል።በመዲናዋ በሚገኙ 298 ት/ ቤቶች
የስፖርት ስልጠናዎች ሊጀመር ነው ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ ከኤሴቅ ዲኮርና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ጋር በዛሬው ዕለት አራት ኪሎ በሚገኘው ወወክማ አዳራሽ ፣ባዘጋጀው የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የስፖርት ፌደሬሽኖች በተገኙበት፣ የጋራ ውይይትና ምክክር ተካሄደ፡፡ በዚህ ዝግጅት በ298 ት/ ቤቶች በ149 የት/ ቤት አዳራሾች የስፖርት ስልጠናዎች እንደሚጀመር የተገለጸ ሲሆን ይህንንም ስራ ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ አሰልጣኞችን በመመደብ፣ ስልጠናው በመስጠት፣ ውድድሮችን በማዘጋጀት እንዲሁም ኤሴቅ ዲኮር እና ኢቨንት ጋናይዘር በትምህርት ቤት ያሉ አዳራሾችን ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ በማዘጋጀት በጋራ እንደሚያከናውኑት ተጠቁሟል፡፡ የውይይቱና ምክክሩ ዋነኛ አላማ ፣ ሁሉም የቴኳንዶ፣ የማርሻል አርት ባለሙያዎች በጋራ ሆነው እየተመካከሩ በመስራት ይህን የስፖርት ዘርፍ ለማጠናከርና ከፍተኛ ተሰጥቶት በማህበረሰቡ ዘንድ ተወዳጅ እንዲሆን ማስቻል ነው። ኤሴቅ ዲኮር እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር “ ትምህርት ለትውልድ“ በሚል መርህ፣ ከሃምሌ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወጣቶችን ከተለያዩ ሱሶችና ከአልባሌ ቦታ ለመጠበቅ አቅዶ በመነሳት፣ ከት/ሚር ስምምነት በመፈጸም ወደ ስራ የገባ መንግስታዊ ያልሆነ የግል ድርጅት ነው
ተብሏል።

Read 465 times