በረቡኒ፣ መባ፣ ከዕለታት፣ ጢባጢቤና በሌሎችም ፊልሞቿ አድናቆትን ያተረፈችው ደራሲና ዳይሬክተር
ቅድስት ይልማ ስራ የሆነውና “ሰላም ነው?” የሚል መጠሪያ የተሰጠው ፊልም ከነገ በስቲያ በብሔራዊ
ቴአትር አዳራሽ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ ይመረቃል፡፡ የ1፡25 ሰዓት ርዝማኔ ያለውና የፍቅር ኮሜዲ
ዘውግ ያለው ፊልሙ የሰውን እድሜና እድል የሰረቀ ሰው በምንና እንዴት ይቀጣል በሚለው ላይ
እንደሚያጠነጥን የፊልሙ ፕሮዲዩሰር ፀጋነሽ ሃይሉ እና የሌሊያና ፊልም ፕሮዳክሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ
ተናግራለች፡፡ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አንድ አመት የፈጀ ሲሆን በፊልሙ ላይ ፀጋነሽ ሃይሉ ኤርሚያስ
ታደሰ አስኒክ በቀለ፣ ቴዎድሮስ ወዳጄና ሌሎችም አንጋፋና ወጣት ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና