የጋዜጠኛና ደራሲ ተሾመ ገብረሥላሴ “ባልታሰሩ ክንፎች” የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በዋቢሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡
መጽሐፉ፤ ወጐችን ተረኮችን፣ የታሪክ ማስታወሻዎችን፣ ዝርው ግጥሞችንና አጭር ልብወለዶችን ያካተተ ሆኖ በ184 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን በ60 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
“ጋዜጠኝነትን ሙያዬ ብዬ የጀመርኩት በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ነው” ያለው ተሾመ፤ ከዚያም በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት፣ በሸገር ሬዲዮና በሌሎች መገናኛ ብዙሃን ፕሮግራሞችና አምዶችን ከአዘጋጅነት እስከ አርታኢነት እንደሰራ ይናገራል፡፡
ደራሲው “የባህር ጠብታ” የተሰኘውን የመጀመሪያ መጽሐፉን ከ10 ዓመት በፊት ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና