“የማይታየውን በሚታይ” በሚል ርዕስ በጋለሪያ ቶሞካ ለወር ያህል ለተመልካች ክፍት ሆኖ በቆየው የስዕል ትርኢት ላይ ነገ ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ውይይት እንደሚካሄድ ተገለፀ፡፡ በአውደ ርዕዩ የወጣቱ ሰዓሊ ኪሩቤል አበበ ከ35 በላይ የስዕል ስራዎች የቀረቡበት ሲሆን ውይይቱ በሰዓሊው የአሳሳል ዘይቤ፣ ፍልስፍናና በስዕሎቹ ላይ እንደሚያተኩር የተናገሩት የጋለሪው ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ነብዩ ግርማ፤ የስዕል ትርኢቱም ለተጨማሪ አንድ ወር ለተመልካች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ አክለው ገልፀዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና