በደራሲ ዘውዱ አበጋዝ ተተርጉሞ በተሻለ አሰፋ የተዘጋጀው “ቆንጆዎቹ” የተሰኘ ቲያትር ከ15 አመታት በኋላ ወደ መድረክ የተመለሰ ሲሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ ለተመልካች ይቀርባል፡፡
በስደት ህይወት ላይ የሚያጠነጥነውና የታችኛውን የህብረተሰብ ክፍል ይዳስሳል የተባለው ይኸው ቲያትር፤ የ2፡15 ርዝማኔ እንዳለው ታውቋል፡፡ በቲያትሩ ላይ ወለላ አሰፋ፣ ትእግስት ግርማ፣ ሰለሞን ሐጐስ፣ ይገረም ደጀኔና ሕሊና ሲሳይን ጨምሮ ሌሎች አንጋፋ ተዋንያን ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና