Saturday, 19 December 2015 10:48

“ቆንጆዎቹ” ከ15 አመታት በኋላ ወደ መድረክ ተመለሰ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በደራሲ ዘውዱ አበጋዝ ተተርጉሞ በተሻለ አሰፋ የተዘጋጀው “ቆንጆዎቹ” የተሰኘ ቲያትር ከ15 አመታት በኋላ ወደ መድረክ የተመለሰ ሲሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ ለተመልካች ይቀርባል፡፡
በስደት ህይወት ላይ የሚያጠነጥነውና የታችኛውን የህብረተሰብ ክፍል ይዳስሳል የተባለው ይኸው ቲያትር፤ የ2፡15 ርዝማኔ እንዳለው ታውቋል፡፡ በቲያትሩ ላይ ወለላ አሰፋ፣ ትእግስት ግርማ፣ ሰለሞን ሐጐስ፣ ይገረም ደጀኔና ሕሊና ሲሳይን ጨምሮ ሌሎች አንጋፋ ተዋንያን ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

Read 1572 times