የደራሲ ኤልያስ ማሞ “እንጦሽ”፣ “ውቤ ከረሜላ -1” እና “ጉጉት” የተሰኙ ሶስት መፃህፍት ነገ ጠዋት በ 4 ሰዓት በብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃህፍት ኤጀንሲ አዳራሽ ይመረቃሉ፡፡
“እንጦሽ” በ2006 ዓ.ም ለንባብ የበቃ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ ሲሆን “ውቤ ከረሜላ - 1” የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮችን የሚዳስስ መፅሀፍ ነው፡፡ በነገው እለት ለንባብ የሚበቃው “ጉጉት”፤ የ“ውቤ ከረሜላ” ሁለተኛ ክፍል እንደሆነ ታውቋል፡፡
ሶስቱም መፃህፍት እያንዳንዳቸው ከ230 ገፆች በላይ ያሏቸው ሲሆን “እንጦሽ” በ48 ብር፣ “ውቤ ከረሜላ” በ50 ብር እንዲሁም “ጉጉት” በ60 ብር ለገበያ መቅረባቸው ተገልጿል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና