በሻሸመኔ ከተማ እና አካባቢዋ ኪነጥበባት አፍቃሪዎች የተቋቋመው “ከአድማስ ፊት” የኪነጥበብ ማህበር 43ኛ ወርሃዊ ዝግጅቱን እና የተመሰረበትን አምስተኛ አመት እንደሚያከብር አስታወቀ፡፡ ነገ ከሰዓት በኋላ በከተማዋ ሁለገብ አዳራሽ በማህበሩ አባላት እና የአካባቢው ማህበረሰብ በተጨማሪ አርቲስት ሜሮን ጌትነት እና አርቲስት ዘላለም ኩራባቸው በክብር እንግድነት ይገኛሉ፡፡ በዝግጅቱ የማህበሩን የአምስት ዓመት ጉዞ የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም የሚቀርብ ሲሆን ሽልማት የሚያሰጥ የግጥም ውድድርም ይኖራል፡፡