አንዱአለም ተገኝ ወደ ሳኡዲ አረቢያ የሄደው 20ሺ ብር ለኤጀንሲ ከፍሎ እንደሆነ ይናገራል -ለተለያዩ የግል ወጪዎቹም 5ሺ ብር አውጥቷል፡፡ ይሄን ሁሉ ገንዘብ ያወጣው ሳኡዲ አረቢያ በሹፍርና እንደሚቀጠርና ደሞዙም 28ሺ ብር እንደሆነ ከኤጀንሲው ስለተነገረው እንደነበር ይገልፃል፡፡ ሆኖም እዚያ ሲደርስ ቃል የተገባለትን አላገኘም፡፡ “ያገኘሁት ስራ ገጠር ውስጥ የእርሻ መኪና ላይ ነበር፣ እሱን ደግሞ አልቻልኩትም፡፡ ከዚያም በሁለት መቶ ዶላር ላሞችን የማለብ ስራ አግኝቼ ስሰራ ብቆይም ከአቅሜ በላይ ሲሆንብኝ ጥየው መጣሁ” ብሏል፡፡ እዚህ ሲመጣ ደግሞ ሌላ ችግር እንደገጠመው ይናገራል፡፡ “ኤጀንሲዬ ያወጣሁትን ወጪ ክፈል ብሎ ዋሴን ይዞብኛል” ያለው አንዱአለም፤መፍትሔ ፍለጋም ወደ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምጣቱን ገልጿል፡፡

Published in ዜና

አንዳንድ ተረቶች ካልተደጋገሙ አይሰሙም፡፡ “ተናገርን ማንም ስለማይሰማ፤ ደግመን እንናገረዋለን” ብሏል አንድ ፀሐፊ፡፡ (We said it; as no one listens, we will say it again) አወጋጉን እንለውጠው እንጂ ወጉ የዱሯችን ነው!
ከዕለታት አንድ ቀን ሁለት ደገኞች ጐረቤታሞች ነበሩ ይባላል፡፡ የኑሮ እሽክርክሪት አልለወጥ ብሏቸዋል፡፡ ያርሳሉ፤ ያርሳሉ፤ ያርሳሉ፡፡ ኑሮ አልገፋ አላቸው፡፡ እንደውም አንዳንዴ እየከፋ፣ እየባሰ ይመጣ ጀምሯል፡፡
ከጥቂት ጊዜ በኋላ አንደኛው ገበሬ በድንገት በልጽጐ ታየ፡፡

Published in ርዕሰ አንቀፅ

ከ31 ዓመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ የበቃው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከፍተኛ ድጋፍ በስታድዬም ያገኛሉ ተብለው ከሚጠበቁት ብሔራዊ ቡድኖች አንዱ ሆኗል፡፡ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ከ40ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ቡድኑን ለመደገፍ ከፍተኛ እንቅሰቃሴ በማድረግ ላይ መሆናቸው እየተገለፀ ይገኛል፡፡ ይህም ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከዛምቢያና ከአንጓላ ቀጥሎ በአፍሪካ ዋንጫው በከፍተኛ ደረጃ ድጋፍ ሊያገኙ ከሚችሉት አገራት ጋር ያሳልፋታል፡፡ የ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅ ኮሚቴ ከሳምንት በፊት ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት ኢትዮጵያ ለውድድሩ በቀረቡ ትኬቶች ግዢ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ናት፡፡

ምድብ 3 በተለያዩ ትንበያዎች እና አስተያየቶች
በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እጅግ ከተጠበቁ የፍፃሜ ጨዋታዎች ናይጄርያ ከጋና፤ ደቡብ አፍሪካ ከአይቬሪኮስት እና ጋና ከአይቬሪኮስት ዋናዎቹ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ለዋንጫ ቅርብ መሆናቸው የተነገረላቸው ደግሞ ናይጀሪያ፣ ቱኒዚያ፣ ሞሮኮ፣ ዲ.ሪ ኮንጐ እና አንጐላ ናቸው፡፡ በዋናነት ለዋንጫ ድል የተጠበቁት ግን ጋና፣ ኮትዲቯር፣ ደቡብ አፍሪካና ዛምቢያ ናቸው። በምድብ ድልድሉ የሞት ምድብ የተባለው በምድብ 4 ኮትዲቯር፤ ቱኒዝያ፤ አልጄርያና ቶጎ የተገናኙበት ነው። የአይቬሪኮስት አሰልጣኝ ሳብሪ ላሙቺ ለ29ኛው ለአፍሪካ ዋንጫ ድል አድራጊነት የተጠበቀው ቡድናቸው ምንም እንኳን በሞት ምድብ ውስጥ ቢገኝም የተሰጠውን ግምት ለማሳካት አቅም እንዳለው ይናገራሉ፡፡ ዲድዬር ድሮግባ በበኩሉ “ቡድኖች እኛን መግጠም ይፈራሉ፡፡

የኦስካር ሽልማት ከወር በኋላ የሚካሄድ ሲሆን ለሽልማት የሚፎካከሩት እጩዎች ሰሞኑን እንደሚገለፁ ይጠበቃል፡፡የስቴቨን ስፒልበርግ ፊልም “ሊንከን” እና የቤን አፍሌክ ፊልም “አርጎ” በዘንድሮው የኦስካር ሽልማት በበርካታ ዘርፎች የመታጨት እድላቸው ሰፊ መሆኑን ዩኤስኤ ቱዴይ ዘግቧል፡ በሌላ በኩል 70ኛው የጎልደን ግሎብ አዋርድ ከሳምንት በኋላ በካሊፎርንያ ቤቨርሊ ሂልስ በሚገኘው የቤቨርሊ ሆቴል ይከናወናል፡፡ ለዚሁ ሽልማት የቀረቡ እጩዎች ከወር በፊት ይፋ የተደረጉ ሲሆን የሽልማት ስነስርዓቱ የኦስካር አሸናፊዎችን ፍንጭ ሊሰጥ ይችላል ተብሏል፡፡

በዘንድሮ የፈረንጆች ዓመት የኮንሰርት ገቢ የፖፕ ሙዚቃ ንግስቷ ማዶና በአንደኝነት እንደምትመራ ፎርብስ መፅሄት አስታወቀ፡፡ ሊጠናቀቅ ሁለት ቀናት ብቻ በቀረው 2012 ዓ.ም ሙሉ ለሙሉ ትኬታቸው የተሸጡ 72 ኮንሰርቶችን በመላው ዓለም ያደረገችው ማዶና፤ በአጠቃላይ 1ሚ.635ሺ176 ታዳሚዎችን በማዝናናት 228.4 ሚ. ዶላር ገቢ አድርጋለች፡፡

እኔ ታዋቂ በሆነው የእስራኤል የህክምና ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተምሬ በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቅሁ ሃኪም ሆኜ ሳለ፣ እዚሁ ቤርሽባ ከተማ በሚገኘው የሶርኮ ሆስፒታል ውስጥ እንድሠራ የተመደብኩት ግን በሀኪምነት ሳይሆን ህሙማንን ከበር ተቀብዬ እንዳስተናግድ ብቻ ነበር--”
ቤተእስራኤላዊ ዶክተር
ካለፈው የቀጠለ
የእስራኤል የአዲስ መጤዎችና የውህደት ሚኒስትር የሆኑት ሶፋ ላንድቨር፤ ቤተእስራኤላውያን እየደረሠባቸው ያለውን የዘርና የቀለም መድልዎ በመቃወም ድምፃቸውን ማሠማት መጀመራቸዉንና የተለያዩ የመብት ጥያቄዎቻቸውንም ለእስራኤል መንግስት ማቅረባቸውን የቆጠሩት፣የእስራኤል መንግስት ከከበረ ድንጋይ ያሠራውን ድንቅና ውድ የአንገት ጌጥ ምንነቱንና ዋጋውን ጨርሳ ለማታውቀው ሰጐን እንዳሠረላት አድርገው ነው፡፡

Published in ከአለም ዙሪያ

የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር በአገሪቱ በሚረቀቀው አዲስ ህገ መንግስት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ እንዲሳተፉ ጥሪ አቀረቡ፡፡ አልበሽር ሰሞኑን ለተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ መሳሪያ ለታጠቁ ሃይሎች እና የሲቪል ማህበር ድርጅቶች ባቀረቡት ጥሪ፣ “አሁን መተባበር ያቃተን በውስጣዊ ችግሮቻችን ላይ ነው፣ አገራችን በጣም ሰፊ ናት፣ ለሁላችንም ትበቃለች፣ ስለዚህ መሳሪያ መሸከም አያስፈልግም፣ አገራችን እንዴት መመራት እንዳለባት በጋራ እንወስን” ብለዋል፡፡ በህገ መንግስት ማርቀቅ ሂደቱ ላይ ማንም ወገን አይገፋም ያሉት አልበሽር፣ ህገመንግስቱ የሁሉንም ወገኖች ይሁንታ የሚያገኝ እንደሚሆንም ገልፀዋል፡፡

Published in ከአለም ዙሪያ

የህጻናትን ጤንነት እና እድገት የሚፈታተኑ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ለተወለዱ ሕጻናት ጥሩ የሆነ እድገት አስተዋጽኦ ከሚያደርጉት ነገሮች ፍቅር የተሞላው ወላጅነት... ሓላፊነት የተሞላው የቅርብ ክትትል ማድረግ... የተመጣጠነ ምግብ መመገብ... ምቹ የሆነ የአየር ጸባይ... ጥሩ የእረፍት ጊዜ እንዲያገኝ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡ የተወለዱ ጨቅላ ሕጻናት በእድገታቸው ዘመን ጤናማ እንዲሆኑ ገና ከጅምሩ ጥሩ ክትትል ያስፈልጋቸዋል፡፡ ጨቅላዎቹ በአካባቢያቸው ሊፈጠሩ ለሚችሉ ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ሁሉ እንዳይጋለጡ ተገቢው ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል፡፡

Published in ላንተና ላንቺ

ወደ ኋላ አይተን ለምን ፊት አንሆንም?
ያን ለማድረግ እኮ ምንም አላጣንም!
የበሀ ድንጋዮች በምድር ሮሐ፣
ፀሐይ ይንቃቃሉ እስኪጠሙ ውሀ፣
ጐቦዱራ መንደር ድንጋዮች እንዳሉ፣
“የእንቅልፍ ዘመናት መጡብን!” እያሉ፣
ጠራቢ ፍለጋ ያማትራሉ አሉ፡፡
ድሬ ሼህ ሁሴን ላይ የኖራ ምሥጢሩ፣
ይተርፍ የለም እንዴ ለሀገር ለምድሩ!?
(“ድንጋይ መፅሐፍ ነው”)

Published in ጥበብ
Page 9 of 11