የገና ጥቁር እንግዳ
እንግዳ መሆን እንዴት ደስ ይላል? እኛ ከመቶ በላይ የምንሆን የዲላ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን የሁለተኛ እና የሶስተኛ ዓመት ተማሪዎች በአዲስ አበባ የሚገኙ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንግዶች ለመሆን ከአንድ ወር በላይ ስንዘጋጅ ቆይተናል፡፡ በንድፈ ሃሳብ የተማርነውን ጋዜጠኝነት በተግባር ልናየው፤ነገ ባለቤቶቹ የምንሆንበትን ሙያ በእንግድነት ልንጐበኘው፤ታሕሳስ 19 ቀን 2005 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡40 ላይ በሶስት መምህራኖቻችን ፊታውራሪነት በሁለት ሽንጠ ረጃጅም አውቶብሶች ተሰይመን ጉዞአችንን ጀመርን፡፡
ከመነሻችን የጌዴኦ ዞኗ ዲላ ከተማ የሲዳማዎቹን ጩኮ፣ ይርጋለም አፖስቶን ጨምሮ ሌሎች ትናንሽ የገጠር ከተሞች አቆራርጠን ሃዋሳ ለመድረስ ከሁለት ሰዓት ያልበለጠ ጊዜ ነበር የፈጀብን፡፡ ሻሸመኔ፣ ዝዋይ፣ መቂን ጨምሮ የምዕራብ አርሲ እና የደቡብ ሸዋ ከተሞችን አቆርጠን አዳማ ለመግባት፣ ሞጆን ወደ ግራ ትተን ቀኛችንን ስንይዝ፣ ፀሐይዋ የማደሪያዋን በር ለማንኳኳት እጇን ሰድዳ ነበር፡፡
“ከሳቅህ ዓለም አብሮህ ይስቃል፡፡
ከአንኮራፋህ ብቻህን ትተኛለህ!” - ኖዌል ካዋርድ
የሀገራችን ደራሲና ተርጓሚ የሆነ ፀሐፊ በቅርቡ የስኮትላንዳውያንን ባህሪ አስመልክቶ ባሳተመው ቁም ነገር - አዘል የቀልድ መጽሐፍ የሚከተለው ይገኝበታል
ስኮትላንዳዊው በጣም ተቸግሯል፡፡ የንግድ ሥራው ተሰነካክሎ ከፍተኛ የፋይናንስ ቀውስ ውስጥ ነበር፡
በቀቢፀ - ተስፋ ተውጦ ፈጣሪውን፣
“እባክህን እርዳኝ፤ የመጠጥ ግሮሰሪዬ ተሸጠ፡፡
ኢቴቪ በገና በዓል ሰርፕራይዝ አደረገን! ለፋሲካስ?
“አሁን ያለወትዋች የቴሌቪዥን ግብር እንከፍላለን” የኢቴቪ ተመልካቾች
በቀጥታ ወደ ፖለቲካ ወጋችን ከመዝለቄ በፊት ሰሞኑን ከአንድ ወዳጄ የሰማሁትን ቀልድ ላካፍላችሁ አንድ የአገር ውስጥ ጋዜጠኛ ለቀድሞው ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ (ነፍሳቸውን ይማረውና) ጥያቄ ያቀርብላቸዋል፡፡
ጋዜጠኛው - “እስቲ በጣም ያዘኑባቸውን ጊዜያት ይንገሩኝ--” አቶ መለስ - “በህይወቴ በጣም ያዘንኩት ሁለት ጊዜ ነው - ህወኀት ሲከፋፈልና አርቲስቶችን ያነጋገርኩ ጊዜ!”
ክቡር ሚኒስቴር በመልስዎ ውስጥ ያልነገሩን መልሶች
ሙሼ ሰሙ (የኢዴፓ ፕሬዚዳንት)
ላለፉት ስምንት ዓመታት ለመሰረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት የሰጠው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ልማትንም ሆነ እድገት በማያወላዳ መልኩ ማረጋገጥ አልቻለም፡፡ አወዛጋቢ ቢሆኑም ኢኮኖሚያችን ላለፉት ስምንት ዓመታት ከአምስት ፐርስንት አጠቃላይ ዓመታዊ ምርት እድገት ተነስቶ አሁን ወደ አስር ፐርሰንትና ከዛም በላይ እንዳደገ በርካታ ዋቢዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡
ይህም ሆኖ እድገቱ ያስከተለው ኢኮኖሚያዊ ለውጥ እንደሚወራለት የመሰረተ ልማት፣ የገበያ ትስስርና የምርታማነትን ችግር ፈቶ የኢኮኖሚዊ መዋቅር ሽግግርን በአስተማማኝ ሁኔታ በማረጋገጥ እድገቱ (Growth) በሂደት ወደ ልማት (Development) ተስፋፍቶ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል የሚችል አስተማማኝ ኢኮኖሚ መሆኑን ማረጋገጥ አለመቻሉ የብዙዎቻችን ጥያቄና የሃገሪቱ ፈተና እንደሆነ መቀጠሉ ግልጽ ነው፡፡
ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ከጌታ መንገድና ከኢህአዴግ መንገድ አንዱን መምረጥ ይኖርባቸዋል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨረቃን ከሰማይ አውርዱልን እያለ አይደለም። የኢትዮጵያ ሕዝብ እያለ ያለው ግልጽነትን፣ ቀጥተኝነትን፣ ቅንነትንና ሀቀኝነትን አውርዱልን ነው። ዴሞክራሲን አውርዱልን ነው። ቁሳዊ ልማት ብቻውን አይበቃም፣ ሰብአዊና መንፈሳዊ ልማትንም አውርዱልን ነው።
ዶ/ር ኃይሉ አርአያ
የጌታ ኢየሱስ መንገድ ስል የክርስትና ሃይማኖት ዕምነት ቀኖናውን (ዶግማውን) ሳይሆን ክርስቶስ በዚህ ምድር ላይ ሲያስተምር ያሳየውን የቀናነት፣ የሃቀኝነት፣ የግልጽነት፣ የፍትሓዊነት፣ የእኩልነት፣ የአንድነት፣ የነፃነት፣ የዴሞክራሲያዊነት፣ የመተሳሰብ፣ የመፈቃቀር፣የመከባበር፣ የመተማመን... መንገድ ማለቴ ነው። ይህ መንገድ የክርስትና ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን የእስልምና እንዲሁም የሌሎች የዓለም ታላላቅ ሃይማኖቶች መንገድ ነው።
ከ800ሺ ብር በላይ የሚያወጣ የቤቶች
ልማት ጽ/ቤት ንብረት ተዘርፏል
በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤት ለግንባታ የሚያገለግሉ ብረቶች በተደጋጋሚ መዘረፋቸውን የተናገሩት የጽ/ቤቱ የቀድሞ ንብረት ቁጥጥር ሠራተኛ ወ/ሮ አልማዝ ወ/አማኑኤል፤ ከ800ሺ ብር በላይ የሚያወጣ የፅ/ቤቱ ንብረት ቢዘረፍም እስካሁን ጉዳዩ በሃላፊዎች ቸልተኝነት እልባት እንዳላገኘ ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡
ንብረቶቹ በተደጋጋሚ የተዘረፉት ረጲ ከሚገኘው የጽ/ቤቱ ዋና መጋዘን እንደሆነ የገለፁት ወ/ሮ አልማዝ፤ንብረቶቹ ቆጠራ እንዲካሄድባቸው እንዲሁም ያለውና የጠፋው ተለይቶ እንዲታወቅ ለፕሮጀክቱ ጽ/ቤት በደብዳቤ ማሳወቃቸውን ይናገራሉ፡፡
አዲስ አበባ በህገወጥ ልማዶችና የወሲብ ድርጊቶች እየተናጠች ነው
ግብረሰዶም ከሚገመተው በላይ በከፍተኛ መጠን እየተስፋፋ ነው
አብዛኞቹ የከተማዋ ማሳጅ ቤቶች የወሲብ ንግድ እንደሚያጧጡፉ ታውቋል
ከ3600 በላይ ህገወጥ ልማዶችና የወሲብ ድርጊቶች የሚፈፀምባቸው ቤቶች አሉ
ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ፖሊሶችና ነጋዴዎች የአነቃቂ እፆች ተጠቃሚ ናቸው
በእርቃን ጭፈራ ቤቶች ደጃፍ ከሚቆሙ መኪኖች አብዛኛዎቹ የመንግስትና የንግድ ታርጋ የለጠፉ ናቸው
በአዲስ አበባ ህገወጥ ተግባራት የሚከናወኑባቸው ቤቶች በከፍተኛ መጠን እየጨመሩ መምጣታቸውንና ከተማዋ አደጋ ላይ እንደሆነች ሰሞኑን ይፋ የተደረገ ጥናት አረጋገጠ፡፡
የገና እለት ከቧንቧ የፈሰሰው “ደም” ሰፈርተኛውን አደናገጠ
በተለምዶ አጠራሩ አስራ ስምንት ልኳንዶ 07 ሰፈር በሚባለው አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች የገና በአል እለት ውሃ ከሚቀዱበት ባንቧ ድንገት ደም በመፍሰሱ መደናገጣቸውን ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ የአካባቢው ውሀ ለሁለትና ለሦስት ቀን እንደሚጠፋ የገለፁት የአካባቢው ነዋሪ ወ/ት ህይወት መለሠ፤የገና በአል ሰሞን ውሃ ሳይጠፋ መቆየቱንና የበዓሉ እለት ጠዋት ላይ ውሀ ሲቀዱ ከቧንቧው ደም መሠል ነገር በመፍሰሱ መደናገጣቸውን ይናገራሉ፡፡ የእሳቸው ቤት ቧንቧ ብቻ መስሏቸው እንደነበር የገለፁት ወ/ት መሠል፤ በኋላ ግን ጐረቤቶቻቸውም ተመሳሳይ ነገር እንደገጠማቸው ማወቃቸውን ተናግረዋል፡ቀዩ ፈሳሽ ለሁለት ቀናት ከቧንቧው ይፈስ እንደነበር ጠቁመው አሁን የጠራ ውሃ ቢመጣም በቧንቧው ውሃ ለመጠቀም ውስጣቸው እሺ እንዳላላቸው ይገልፃሉ፡፡
የቅ/ሲኖዶስ አስቸኳይ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ሰኞ ይጀመራል
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባውን የፊታችን ሰኞ፣ እንደሚያካሂድ ተገለጸ፡፡ በሲኖዶሱ አቸስኳይ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ፣ በሀገር ውስጥ እና በሰሜን አሜሪካ በስደት በሚገኙት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መካከል በተጀመረው የዕርቅና ሰላም ውይይት ቀጣይነት ላይ በመነጋገር ዐቢይ ትርጉም ያለው ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አዲስ አድማስ ከጠቅላይ ቤተክህነቱ ምንጮች እንደተረዳው፤ ሲኖዶሱ በዕርቅና ሰላም ውይይቱ ቀጣይነት ላይ የሚወያየው፣ ከኅዳር 26-30 ቀን 2005 ዓ.ም በዳላስ ቴክሳስ በተካሄደው የዕርቀ ሰላም ጉባኤ የተሳተፈው ልኡክ በሚያቀርበው ሪፖርት ላይ በመመሥረት ነው፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ በአዲስ አበባ በማስተርስ ደረጃ ማስተማር የሚያስችለው ስምምነት ተፈራረመ
ጅማ ዩኒቨርሲቲ በአዲስ አበባ በህብረተሰብ ጤናና በቢዝነስ አስተዳደር በማስተርስ ደረጃ ለማስተማር የሚያስችለው ስምምነት ትናንት ተፈራረመ፡፡ ዩኒቨርሲቲው የስምምነት ሰነዱን የተፈራረመው ኤቢኤች ሰርቪስ ከተባለና በስልጠና፣ በጥናትና ምርምር፣ በጤናና በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፎች እንዲሁም በፕሮግራምና ፕሮጀክት ትግበራ ላይ ከሚሠራ የግል ኩባንያ ጋር ነው፡፡
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍቅሬ ለሜሳና የኤቢኤች ሰርቪስ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ማርቆስ ፈለቀ፤ የስምምነት ሰነዱን ትናንት በሸራተን አዲስ በተካሄደ ስነ ስርዓት ተፈራርመዋል፡፡