Saturday, 02 July 2016 13:20

የኒውዚላንዷ ከተማ ሰራተኛ ቸግሮኛል አለች

Written by 
Rate this item
(4 votes)

የከተማዋ ስራ አጦች ሁለት ወጣቶች ብቻ ናቸው

   ኬታንጋታ የተባለቺውና 800 ነዋሪዎች ብቻ ያሏት የኒውዚላንድ ከተማ “እጅግ ብዙ ክፍት የስራ ቦታና አነስተኛ ዋጋ ያላቸው የመኖሪያ ቤቶች ቢኖሩኝም፣ ይህን ዕድል የሚጠቀምበት ሰው አጥቼ ተቸግሬያለሁ፣ እባካችሁ ኑ ወደ እኔ” ማለቷን ቢቢሲ ዘገበ፡፡ የሰው ሃይል እጥረት ያጋጠመው የከተማዋ አስተዳደር ችግሩን ለመቅረፍ፣ የሌሎች የኒውዚላንድ ከተሞች ነዋሪዎችን እባካችሁ ኑልን ሲል ጥሪ ያሰተላለፈ ሲሆን፣ የከተማዋ የስራ አጦች ቁጥር 2 ብቻ ነው ሲሉ ከንቲባው ማስታወቃቸውንም ገልጧል፡፡ ከንቲባው ወደ ከተማዋ ለሚመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች፣ የመኖሪያ ቤት በእጅግ አነስተኛ ዋጋ ከማቅረብ ባለፈ፣ሌሎች በርካታ ማበረታቻዎችን ለማድረግ ማቀዳቸውንም አስታውቀዋል፡፡ በከተማዋ ካሉ ክፍት የስራ ቦታዎች መካከል የመነሻ ደመወዛቸው እስከ 26ሺህ 500 ፓውንድ የሚደርሱ እንደሚገኙበት የጠቆመው ዘገባው፤ አስተዳደሩ በህክምና፣ በህንጻ ግንባታ፣ በወታደራዊ ሃይልና በሌሎች በርካታ ዘርፎች ያሉትን ክፍት የስራ ቦታዎች ዝርዝር ይፋ ማድረጉንም ገልጧል፡፡

Read 2178 times