አንድ አባትና ትንሽ ልጁ፣ በዱር እንስሳ
መጠበቂያ (zoo) ውስጥ ነብር በሚንጎራደድበት
የብረት ፍርግርግ ፊት ለፊት ቆመዋል፡፡ አባት
ለልጁ ነብር ምን ያህል ሃይለኛና ጉልበተኛ
እንስሳ እ ንደሆነ ያ ስረዳዋል፡፡ ል ጅም ኮ ስተር
ብሎ አባቱ የሚለውን በትኩረት ሲሰማ ቆየና፤
“አባዬ” አለ በመጨረሻ፤ “አባዬ፤ነብሩ
ከብረቱ ወጥቶ ከበላህ ---”-
“እ ---ልጄ ከብረቱ ወጥቶ ከበላኝ ----
ምን?” ሲል ጠየቀው፤ የሚለውን ለመስማት
ጓጉቶ፡፡
ልጅም፤ “ወደ ቤት የሚወስደኝ አውቶብስ
ስንት ቁጥር ነው?”
Published in
ጥበብ