Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

አንድ የሀይማኖት ሰው አንዲት ወዳጅ ነበረቻቸው፡፡ የብዙ ልጆች እናት ናት!

ለመስበክም፣ ለጨዋታም ወደዚች ሴት ዘንድ ብቅ ሲሉ ክፉኛ ልባቸው ይነካል፡፡ እናም ለአንዳንድ የቅርብ ሰዎቻቸው ሲገልፁዋት፤ “ባተ-ተረከዟ ይቆጡኛል ያለ የተቀጣ፣ ዳሌ ሽንጧ ግራ ቀኝ ሲል ሰልፍ የሚያስከብር፣ ዐይኗ አንዴ እሚያባባ አንዴ ወኔ እሚቀሰቅስ፤ ስትስቅ፣ እንኳን ስቃልኝ ምነው በሳቀችብኝና ጥርሷን ባየሁት የምታሰኝ፣ ስብከት ስታዳምጥ ውበቷ የበለጠ የሚደምቅ፣ ወደዚህ ምድር እንድትመጣና እኔ እንዳያት የፈቀደውን አምላክ የበለጠ እንድወደው ያደረገች፤ የቁንጅና ተምሳሌት ነች!” ይላሉ፡፡

የአገር ሽማግሌዎች - “እንደው ንጉሥ ሆይ! ጤናዎን ደህና አደሩ?”

ንጉሥ - “ኧረ ደህና ነኝ! እኔን ያሳሰበኝ የእናንተ ጤና ማጣት ነው! ለእናንተ ስል ካገር በወጣሁ ምን     አሳመማችሁ?!”

- (የኢንዶኔዢያ ምሳሌያዊ አነጋገር)

“የእኛ ሰው እንኳን ከኪሱ ከእድሜህ ላይ ቀንሰህ ጠጣም ቢሉት እሺ ነው የሚለው!”

- የአዲስ አበባ አስተናጋጅ

“የተማረ ይጥረበኝ!” አለች ኮብል - ስቶን

“የምናየው ባለቀለም ቴሌቪዥን (Colour TV የምንኖረው ጥቁርና ነጭ (Black and White)”

- ሀገርኛ አባባሎች

***

አንድ ሰው ለአንድ ወዳጁ እንዲህ ይለዋል፡-

“ለማንም እንዳትነግር፤ አንድ ምስጥር እነግርሃለሁ”

“ለማንም አልነግርም፡፡ ያንተ ምስጥር’ኮ የኔ ሚስጥር ነው” ይላል ወዳጁ፡፡

“ማልልኝ” ይለዋል፡፡

እሺ ብሎ ይምላል ወዳጅ፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ባልና ሚስት ስለኑሮ ውጣ ውረዳቸው ይወያያሉ፡፡ ባል በጣም ጉረኛ ነው፡፡ ሚስት በጣም ትሁት ናት፡፡

ባል ሠፈር-መንደሩ ጀግና እንዲለው “ለሰው ሁሉ ይሄን ጀብዱ ሰርቼ፣ ከእገሌ ተጣልቼ ልክ አስገብቼው፣ እገሌና እገሌ ተጣልተው አስታርቄያቸው፣ የዕድር ሊቀመንበር ጠፍቶ እኔን መርጠውኝ” እያለ ጉራውን ይቸረችራል! ሚስት፤ “ይህ ሁሉ ጉራ አይጠቅምህም! ወይ ልብ ግዛ አሊያ ጉራ አትንዛ!” ባል፤ “ጉራ አይደለም! እንዲያውም በቅርቡ ጠብ የሚፈልገኝ አንድ ሰው አለ፡፡

እንዴት እንደማቀምሰው አሳይሻለሁ!  የሰው ልክ አያውቅም ይሄ የሰው ትንሽ!” ሚስት፤ “ልብም ቢኖርህ፣ ጀግንነትም ቢኖርህ ሳታወራው፣ ሳትጮህ መሥራት አትችልም?” ባል፤

“የሀበሻ ጀብዱ” የሚለው መፅሐፍ ውስጥ የሚከተለው ታሪክ አለ፡፡ እነሆ:-

በጨርቅ ተራ ሁለት ገበያተኞች ይጨቃጨቃሉ፡፡ ጨርቁን የሚገዛው ሰውዬ እጅግ በጣም ረጅም ሲሆን ሻጩ ደግሞ በጣም አጭር ነው፡፡ እናም ገዢ በሚችለው መልኩ ክንዱን ዘርግቶ፣ ጣቶቹን ወጥሮ አስር ክንድ ለካና ምልክት አደረገ፡፡ ሻጩ ደግሞ በሚችለው ሁሉ ጣቶቹን ሳይወጥር እሱም አስር ክንድ ለካና እሱም ምልክት አደረገ፡፡ ሁለቱ በለኩት መካከል ከአንድ ክንድ የሚበልጥ ልዩነት መጣ፡፡ ገዢው ሻጩን፤ አውቆ ክንዱን ሳይወጥር ይለካል ሲል አመረረ፡፡ ሻጩ በምኒልክ እየማለ ሃቀኛ ነጋዴ መሆኑን እግዚአብሔርን ምስክርነት ጠራ፡፡ በዚህ መሃል ብዙ ወሬኛ ገበያተኞች ከበቧቸው፡፡ በነዚህ ወሬኞች ፊት ሁለቱም ደጋግመው ቢለኩም ልዩነቱ ተመሳሳይ ነበር፡፡ እናም መግባባት ባለመቻላቸው ያላቸው ብቸኛ አማራጭ ዳኛ ፍለጋ መሄድ ብቻ ነበርና፣ ሸማቸውን አያይዘውና አቆላልፈው፣ ጐን ለጐን ግራና ቀኝ እጆቻቸውን በነጠላቸው ጫፎች ሸብ አድርገው አስረው፤ ከቋጠሩ በኋላ ወደ የገበያው ሸምጋይ ዳኛ በብዙ ወሬኞች ታጅበው ሄዱ፡፡

(Let’s frustrate together!) አፍሪካዊ ገጣሚ

አንድ ንጉሥ ወደፊት ለልጆቹ ምን ማውረስ እንዳለበት ሲጨነቅ ሲጠበብ ቆይቶ፤ አንድ ቀን አንድ የፍተሻ ፈተና ለልጆቹ ሊሰጥ ይወስንና ልጆቹን ያስጠራቸዋል፡፡

ከዚያም የሚከተለውን ጥያቄ ይጠይቃቸዋል:-

“ልጆቼ! መቼም ‘ዞሮ ዞሮ ከቤት፣ ኖሮ ኖሮ ከመሬት’ የሚቀር የለም፡፡ እኔም እድሜዬ እየገፋ፣ መቃብሬ እየተማሰ፣ መገነዣ ክሬ እየተራሰ ያለ መሆኑን ትገነዘባላችሁ፡፡ ስለሆነም፤ የትኛው ልጄ መንግሥቴን መውረስ እንዳለበት ለመለየት ቀላል ፈተና እሰጣችኋለሁ፡፡ በዚህ ትስማማላችሁ?”

ከዕለታት አንድ ቀን የተራቡ ጅቦች በቡድን ሆነው በጠፍ ጨረቃ ምግብ ፍለጋ ይዘዋወራሉ፡፡ ብዙ ከተጓዙ በኋላ

አንድ ትልቅ ገደል ውስጥ ተንሸራቶ ወድቆ የሞተ ዝሆን ያያሉ፡፡ ገደሉ እጅግ አዘቅት የሆነ ገደል ነው፡፡

ጅቦቹ መመካከር ጀመሩ፡፡

ከፊሎቹ፤

“በረሃብ ከምናልቅ እንግባና ዝሆኑን በልተን ረሀባችንን እናስታግስ” አሉ፡፡

ከፊሎቹ ደግሞ፤

“የለም ጐበዝ! አሁን ስለራበን የሚታየን ሆዳችን ብቻ ነው፡፡ ስንገባ ቁልቁለት ስለሆነ ያለችግር ልንገባ እንችላለን

፡ ገብተን ዝሆኑን ከበላን በኋላ ግን ሆዳችን ይሞላና ቀጥ ያለውን የገደል ዳገት ለመውጣት ፈጽሞ አንችልም፡፡

ይቅርብን፡፡ ሌላ የሚበላ እንስሳ ብንፈልግ ይሻላል” አሉ፡፡

በመጀመሪያ እንግባና እንብላ ያለው ጅብ አሁንም ሙግቱን ቀጠለ:-

“ለዛፍ ሁሉ ያስተማረው ማን ሆነና ነው!” አለው

አለቃ ገብረ ሃና ከዕለታት አንድ ቀን መንገድ እሄዳለሁ ብለው ይነሳሉ፡፡

“ማዘንጊያ” ይላሉ ሚስታቸውን

“አቤት” ይላሉ ሚስት

“መንገድ ልሄድ አስቤያለሁ”

“ወዴት?”

“ወደ ቆላ ወርጄ የታመመ ጠይቄ፣ የተጣላ አስታርቄ እመለሳለሁ!”

“እንግዲያው ባዶ ሆድዎን አይሄዱም ቆይ ቁርስ ደርሷል፡፡”

አንድ የጀርመኖች ተረት እንዲህ ይላል፡፡

አንድ እረኛ በጐችን ለግጦሽ አሰማርቶ በጫካ ውስጥ ሲዘዋወር አንድ የአንበሳ ግልገል ያገኛል፡፡ ከዚያም

እንዲህ ሲል ያስባል (በግርድፉ ግጥሙ እንዲህ ይተረጐማል)

“ይህ ያንበሳ ግልገል፣ ምን አንበሳ ቢሆን

ከበግ ጋር ካደገ፣ ይተዋል ፀባዩን

በጥርሱ መናከስ

በክርኑ መደቆስ

ያየውን ማሳደድ

ዱር ገደል መሰደድ

ጉልበት ለማሳየት

ጧት ማታ ማጋሳት

የጫካው ንጉሥ ነኝ፣ ለማለት ማጓራት

የደኑን አራዊት፣ ስገዱልኝ ማለት

ይህ ሁሉ ይቀራል፣ በግ ሲሆን አንበሳው

ገና ህፃን ሳለ፣ ከበግ ጋር ሳኖረው”

አለና ያ እረኛ፣ ግልገሉን አቀፈው

እየደባበሰ፣ ለማዳ አደረገው፡፡

የዱር አራዊት ንጉሥ አያ አንበሶ አንዳንድ አስቸጋሪ እንስሳትን እየከታተለ ወደ ችሎቱ እንዲያቀርብለት ነብርን ይሾመዋል፡፡

መቼም “ማዘዝ ቁልቁለት ነው” ይባላልና ነብር ደግሞ በበኩሉ ዝንጀሮን የቅርብ ጆሮ ጠባቂው አድርጐ ይሾመዋል፡፡ በየጠዋቱ ነብርና

ዝንጀሮ እየተገናኙ ይወያያሉ፡፡

“እህስ ደኑ እንዴት አደረ?” ይላል ነብር፡፡

“ዛሬ ደህና ነው ያደረው፡፡ በጣም ሰላም ነው” ብሎ ይመልሳል ዝንጀሮ

ሌላ ጠዋት፡፡

“እህስ ደኑ እንዴት አደረ?” ይጠይቃል ነብሮ፡፡