Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ንጉሥ ባለሟሎቻቸውን ይዘው ወደ አንድ ጥቅጥቅ ወዳለ ደን ይሄዳሉ፡፡

ከዚያም፤

“በሉ ዛሬ ዒላማና ማነጣጠር እንወዳደራለን፡፡ የምትፈልጉትን ዒላማ መርጣችሁ ምቱ” አሉ፡፡

በመጀመሪያ አንደኛው ባለሟል፤

“እኔ እዚያ ከሩቅ የሚታየውን ቅንጭብ ለመምታት እፈልጋለሁ” ብሎ አነጣጠረና ተኮሰ፡፡ የቅንጭቡን አንድ ቅርንጫፍ መታ”

ሁለተኛው ባለሟል፤

“እኔ ያንን ረዥም ባህር ዛፍ ነው የምመታው” አለና አልሞ ተኮሰ፡፡ አንዱን ትልቅ የባህርዛፍ ቅርንጫፍ ዘነጠለው፡፡

(“አንተ መሀላ የት ትሄዳለህ” ይላሉ ሽማግሌ

“የማለውን ለመግደል” ይላል መሀላ፡፡“ካጣኸውስ?” ቢሉት፤ “ያስማለውን እገላለሁ” ይላል - (የአማርኛ ተመሳሳዩ)

ህንዶች የሚተርቱት አንድ አፈ - ታሪክ እንዲህ ይላል፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን በአንድ  አካባቢ፣ አንዲት ነብሰ - ጡር እናት፤ ጊዜዋ ደርሶ ኖሮ፣ ሽንት ውሃዋ ፈሶ፣ በምጥ ትያዛለች፡፡

የሠፈር ሰው ሁሉ፤ “እንደምንም በደህና ትገላገል!” ይላል፡፡

“ማርያም ትዳብሳት!”

“ምነው የዛሬ ምጧን በሰላም በተወጣች?” እያለ እንደየአምልኮው ይማጠናል፡፡

“እያንዳንዷ ሩዝ ላይ የሚበላት ሰው ስም ተፅፏል!” - የህንዶች አባባል

በአንድ ወቅት እንደዋዛ ያለፍናቸው ታሪካዊ ክስተቶች ሲቆዩ ተረት ወይም አፈ-ታሪክ ይመስላሉ፡፡

አንድ ጊዜ በሀገራችን እንዲህ ሆነ፡-

በዱሮ ዘመን ነው፡፡ አንድ እውቅና ትልቅ ባለሥልጣን በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ስብሰባ ይጠራሉ፡፡ ሌሎች ባለሥልጣኖች፣ ካድሬዎች፣ ምሁራንና አብዮታዊ ምሁራን አሉ፡፡ (ያኔ “ማህል ሰፋሪዎች”) የሚባሉት ሳይቆጠሩ ነው፡፡

ነብሷን ይማርና፤ ዶሮ እንደዛሬው አልቀመስ ሳትል በፊት፤ በብርም በብር ተሃምሣም ትሸጥ በነበረ ጊዜ፤ የሚከተለውን ተረት ከዓመታት በፊት ተርተነዋል  ለአንድ በዓል ብለን፡፡ ያኔ ያልነውን ላልሰማና ሰምቶ ዝም ላለ ዛሬም መተረቱ አስፈላጊ ሆኖ ነው እንጂ፤ አሁን ቅንጦት ሊመስልብን ይችላል፡፡ እነሆ፡- የዕንቁጣጣሽ ዕለት ነው፡፡ አባትና እናት አንድ ቋሚ ልማድ አላቸው፡፡ በተለይ እንግዳ ከመጣ ልጃቸውን እቆጥ ላይ አውጥተው ያስሩታል፡፡ ልጁምለቅሶውን ይቀጥላል፡፡ ምግቡ ተበልቶ ሲያበቃ ይፈቱና ያወርዱታል፡፡ ይህ እንግዲህ በዓመት በዓል፣ በዓመት በዓል የሚሆን ነገር ነው፡፡ ከዓመት በዓላቱ በአንደኛው ዕንቁጣጣሽ ቀን አንድ እንግዳ ይመጣል፡፡

“ቤቶች?” ይላል፡፡

“ደጆች” ይሉታል፡፡

በምፀታቸው ረቂቅነት የሚታወቁት ፀሀፌ-ተውኔት መንግሥቱ ለማ ስለ አካላዊ እንቅስቃሴ በድራማ ውስጥ ሲያስተምሩ፤ ድራማ ሲሠራማንኛውም የሰውነታችን ክፍል ሊንቀሳቀስ ይገባዋል ለማለት የሚከተለውን ተረት ይጠቅሱ ነበር፡፡ እነሆ፡-

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ለምድር ለሰማይ የከበዱ ዲታ፣ በጣም የሚፈሩ የሚከበሩ ትልቅ ሰው ነበሩ፡፡ እኒህ ሰው ከባለቤታቸው ጋርሲኖሩ አንድ ወንድ ልጅ አፍርተዋል፡፡ ዕድሜ ልኩን ለእሳቸው ሲያገለግል የኖረ ብርቄ የሚባል አገልጋይ ደግሞ አላቸው፡፡ በየጊዜው ግብር ያገባሉ፡፡ ድል ያለ ድግስ ይደግሳሉ፡፡ የከተማውን ታላላቅ ሰዎች ይጠራሉ፡፡ በዚህ የግብር ድግስ ላይ ብርቄ የጌታውንእጅ ባስታጠበ ቁጥር እንዲህ ይላል፡-

አንድ ንጉሥ ሶስቱን ጥበበኛ አማካሪዎቻቸውን ጠርተው፤

የመጀመሪያውን፤ “በጣም በትንሽ ብር ይሄን ቤት የሚሞላ ነገር ገዝተህ ና” ብለው ጠየቁት፡፡

ሁለተኛውን አስቀርበው፤

“ሰውን እንዳይረሳ የሚያደርገው ምን እንደሆነ መርምረህ ንገረኝ” አሉት፡፡

በመጨረሻም ሶስተኛውን ጠርተው፤

“መጽሐፍ ገልጠህ፣ አዋቂ ጠይቀህም ሆነ፣ ከምትወዳቸው ሰዎች ጋር ተማክረህ፤ አንድን ህዝብ ታላቅ የሚያደርገው ምን እንደሆነ እንድትነግረኝ” አሉት፡፡

በርካታ ባለሟሎች፣ ወታደሮችና አማካሪዎች የነበሯቸው አንድ ተዋጊና ጀግና ንጉሥ በ18ኛው ክፍል ዘመን ይኖሩ ነበር ይባላል፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ታላቅ ውጊያ ተዋግተው ሲመለሱ፤ መኳንንቶቹና ወታደሮቹ ሹመት ካልተሰጠን ብለው አስቸገሯቸው፡፡

ንጉሡም እንሾም ያሉትን ሁሉ ሰበሰቡና፤

“በሉ እንግዲህ እያንዳንዳችሁ በምን ምክንያት  ሹመት እንደምትጠይቁ አስረዱኝ?” አሉና ጠየቁ፡፡

ኮነሬሉ ተነስተው፤

“እኔ በእኛ ጦር ውስጥ ከ20 ዓመት በላይ ያገለገልኩ ስለሆነ ሹመት ይገባኛል” አሉ፡፡

(ነገር - የገባት ሰጐን)

አንድ የቱርኮች ተረት እንዲህ ይላል፡-

ከእለታት አንድ ቀን የዱር አራዊቶች ተሰብስበው፤

“የዱር የጫካው ገዢ ንጉሳችን አንበሳ ታሟል፡፡ ነብር ደግሞ እኔ ልግዛችሁ እያለ ይፎክራል፡፡ ምን ብናረግ ይሻላል?” የሚል ጥያቄ አነሱ፡፡

አንደኛው - “ለጌታችን እንደቆምን ለማረጋገጥ እንሂድና ጦርነት እንግጠመው!” አለ

ሁለተኛው - “እሱ በጣም አደገኛ አውሬ ስለሆነ ፊት ለፊት ከመግጠም ይልቅ የሱን አይነት ቆዳ ለብሰን ወገኑ መስለን፣ ሳያስበው እናጥቃው!”

ሦስተኛው - “የለም ወደ ጦርነት ከመግባታችን በፊት አርፎ እንዲቀመጥ እናስጠንቅቀው”

እንደ “ናብሊስ” መጽሐፍ አገላለፅ፤ “ሩቢኮንን ማቋረጥ” የሚለው አባባል ዛሬ ያነጋገር ፈሊጥ ሆኗል፡፡ ወደ ማይመለሱበት ወይም ወደማይሻገር ውሳኔ ላይ ተደረሰ እንደማለት ነው፡፡ ይህ አነጋገር ዕውነተኛ የታሪክ መሠረት አለው፡፡ እነሆ፡-

ጥንት የሮማንና የፈረንሣይን ድንበር የሚለይ ሩቢኮን የሚባል ወንዝ ነበር፡፡ ይህንን ወንዝ ተሻግሮ ወደ ሮም ለመግባት ለራሳቸው ለሮማውያን ጀነራሎች እንኳ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዩ ፈቃድ ያስፈልግ ነበር፡፡ ይህ ፈቃድ ሳይኖር የሩቢኮንን ወንዝ ማቋረጥ ማለት በሮም ላይ ጦርነት እንደማወጅ ይቆጠራል፡፡ ስለዚህ በጥንት ዘመን ጁሊየስ ቄሣር ሠራዊቱን ይዞ ሩቢኮንን በማቋረጡ ከራሷ ከሮም ጋር ፍጥጫ ውስጥ ገብቶ ነበር ይባላል፡፡

“ናብሊስ” የሚለው መጽሐፍ የሚከተለውን ተረት ይነግረናል፡፡

በጥንት ዘመን አንድ በጣም ብልህ ኢትዮጵያዊ ንጉሥ ነበር ይባላል፡፡ በእርሱ ዘመን አንጥረኞች፣ ሸማኔዎች፣ ቆዳ ሠሪዎች፣ የሸክላ ሥራ ባለሙያዎች እጅግ የተከበሩ ባለሙያዎች ነበሩ፡፡ ሀገሪቱ እጅግ ባለፀጋ ህዝቡም ጠግቦ የሚያድር ነበረ፡፡ ይህ ብቻ ግን ንጉሡን በጣም አላረካውም፡፡ አንጥረኞቹ አንድ ግዙፍና ያማረ ደወል አንዲሠሩለት አደረገ፡፡ ይህ ደወል ድምፁ ከሩቅ የሚሰማ ደወል ነው፡፡ በገበያ መካከል በጠንካራ እንጨቶች ላይ እንዲሰቀልና የመደወያው ገመድ እጅግ ዝቅ ብሎ ወደ መሬት እንዲወርድ አስደረገ፡፡ ንጉሡ በአንድ የበዓል ቀን ህዝቡን ሁሉ በደወሉ ዙሪያ ሰብስቦ እንዲህ አላቸው